ሸገር ወሬዎች እና ልዩ ወሬዎች
በድርድር ላይ ያሉት አገር አቀፍ ፓርቲዎች ድርድራቸውን ዛሬ መቀጠላቸው ተነገረ
ኢህአዴግን ጨምሮ 14ቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከ2 አመታት በፊት የጀመሩትን ድርድር ዛሬም እያካሄዱ መሆኑን ተነግሯል፡፡ ፓርቲዎቹ ቀደም ሲል በመረጧቸው 12 የመደራደሪያ ነጥቦች ላይ እየተነጋሩ ነው፡፡ከእነዚህም ውስጥ በ4ቱ ነጥቦች መወያየታቸውና ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል፡፡
የአገሪቱ የምርጫ ህግ የምርጫ ቦርድ አደረጃጀትና የምርጫ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ድርድርም ማሻሻያ በማድረግና ባሉበት እንዲቀጥሉ በመስማማት የመረጧቸው አጀንዳዎች መኖራቸው ይነገራል፡፡ተደራዳሪ ፓርቲዎቹ በሞራል ካሳ ፈንድ፣ በሽብርተኝነት ትርጓሜና በሌሎቹም የፀረ ሽብር አዋጅ አንቀፆች ላይ ማስተካከያ ለማድረግ መግባባት ላይ መድረሳቸው ይነገራል፡፡
ፓርቲዎቹ በፀረ ሽብር ህጉ ላይ ከመግባባት ላይ የደረሱባቸው ጉዳዮች በባለሙያዎች ተደራጅተው እንዲቀርቡ ውሳኔ ማሳለፋቸው ይነገራል፡፡ፓርቲዎቹ ዛሬ የሚያደርጉት ንግግር ተደራጅቶ በሚመጣው ሰነድ ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሰምተናል፡፡
የኔነህ ሲሳይ
የአገሪቱ የምርጫ ህግ የምርጫ ቦርድ አደረጃጀትና የምርጫ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ድርድርም ማሻሻያ በማድረግና ባሉበት እንዲቀጥሉ በመስማማት የመረጧቸው አጀንዳዎች መኖራቸው ይነገራል፡፡ተደራዳሪ ፓርቲዎቹ በሞራል ካሳ ፈንድ፣ በሽብርተኝነት ትርጓሜና በሌሎቹም የፀረ ሽብር አዋጅ አንቀፆች ላይ ማስተካከያ ለማድረግ መግባባት ላይ መድረሳቸው ይነገራል፡፡
ፓርቲዎቹ በፀረ ሽብር ህጉ ላይ ከመግባባት ላይ የደረሱባቸው ጉዳዮች በባለሙያዎች ተደራጅተው እንዲቀርቡ ውሳኔ ማሳለፋቸው ይነገራል፡፡ፓርቲዎቹ ዛሬ የሚያደርጉት ንግግር ተደራጅቶ በሚመጣው ሰነድ ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሰምተናል፡፡
የኔነህ ሲሳይ