ሸገር ወሬዎች እና ልዩ ወሬዎች
በአዲስ አበባ የአቢሲኒያ ባንክ ቴሌ መድሃኒዓለም ቅርንጫፍን ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች ተያዙ

ምንም አይነት ገንዘብ ከቅርንጫፉ እንዳልተዘረፈም አቶ አስቻለው ነግረውናል፡፡ሙከራውን ካደረጉ የተደራጁ ዘራፊዎች የተወሰኑት በዚያው ዕለት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ብለዋል፡፡የተወሰኑት ደግሞ ዛሬ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ነግረውናል፡፡ጉዳዩ በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተካሄደ እንደሚገኝም ሠምተናል፡፡
ከምርመራ ውጤቱ በኋላ ሌሎች ተጨማሪ ግለሰቦች ከሙከራው በስተ ጀርባ መኖር አለመኖራቸው ይታወቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡ባንኩም ምርመራው እንዳበቃ ስለ ጉዳዩ ለህዝቡ ስለ ሁኔታው ያሳውቃል ብለዋል፡፡
ንጋቱ ረጋሳ