ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያሉ ተማሪዎችና ተመራማሪዎች አዳዲስ ምርምርና ፈጠራ አድርገዋል የተባሉ 140 ሰዎች ዘንድሮ ይሸለማሉ ተባለ
ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያሉ ተማሪዎችና ተመራማሪዎች አዳዲስ ምርምርና ፈጠራ አድርገዋል የተባሉ 140 ሰዎች ዘንድሮ ይሸለማሉ ተባለ፡፡
እንዲህ የተባለው ዛሬ በተጀመረውና የፊታችን ቅዳሜ በሚጠናቀቀው 7ተኛ አገር አቀፍ የሣይንሰና ቴክኖሎጂ ኢኖቬሽን ሽልማት መክፈቻ ላይ ነው፡፡
በምክትል ጠቅላይ ሚኒሰትር ደመቀ መኮንን ፕሮግራሙ ዛሬ የተከፈተ ሲሆን እስከ ነገ በተለያዩ ውይይቶች ይቀጥላል፡፡
በሣይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጊቢ ውስጥም አዳዲስ ፈጠራዎች ዛሬ ለእይታ የቀረቡ ሲሆን በባትሪና በፀሐይ ብርሃን የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችም ለእይታ በቅተዋል፡፡
ከነገ በስቲያ ቅዳሜ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ለፈጠራ ባለሙያዎቹ ሽልማት ይበረከትላቸዋል መባሉን ሰምተናል፡፡
ዮሐንስ የኋላወርቅ አስተያየት ይፃፉ (0 አስተያየት)