top of page
በኢትዮጵያ በተለያዩ የትምህርት ተቋማት እንደሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች
ሰኔ 23 2018 በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ14,000 በላይ ጥናቶች እና ምርምሮች በተለያዩ የትምህርት ተቋማት እንደሚደረጉ ይነገራል። ከእነዚህ ጥናቶችና ምርምሮች ስራ ላይ ውለው የህብረተሰቡን ችግር ለመፍታት እያገዙ ያሉት ግን ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል። ጥናቶቹ የህብረተሰቡን ችግር መነሻ አድርገው አለመካሄዳቸው እና በጋራ መድረክ አለመገምገማቸው የችግሩ መነሻ እንደሆነ ተጠቅሷል። በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚገጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በተማሪዎች እና በምሁራን እንዲሁም በተመራማሪዎች የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች በአንድ መድረክ ቀርበው ውይይት ቢደረግባቸው መፍትሄ ያመጣሉ ተብሏል። ይህ የተባለው ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ባካሄደው 18ተኛው የዘርፈ ብዙ ጥናት እና ምርምር ጉባኤ ላይ ነው። በጉባኤው በተለያዩ ዘርፎች ማለትም በቢዝነስ እና ኢንድስትሪ በፋይናስ በግብ
5 hours ago


በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል።
ሰኔ 24/2018 በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል። ከዚህ ቀደም የውጭ ኩባንያዎች ከ49 በመቶ ያልበለጠ ድርሻ ይዘው ከአገር ውስጥ ባለሃብቶች ጋር በጥምረት እንዲሰሩ ነበር የሚፈቀድላቸው። ገደቡ የሎጂስቲከስ ዘርፉ የሚፈለገው ያህል የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ፤ውሳኔውን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ አመልክቷል። ዝርዝር የህግ ማዕቀፎችን የማጠናቀቅ ስራ በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት በኩል እየተከወነ እንደሚገኝም ጠቅሷል። የኢትዮጵያ የሎጅስቲክስ አገልግሎት አሰጣጥ ዝቅተኛ እንደሆነ በየጊዜው የሚወጡ የአለም ባነክ ሪፖርቶች ያሳያሉ የሚሉት ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሎጂስቲክስ እና የንግድ ሠንሠለት ማኔጅመንት ክፍል መምህር ፕሮ
6 hours ago


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው መ/ቤቶች የተገኘባቸውን የኦዲት ከፍተቶች በ10 የስራ ቀናት ውስጥ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ፡፡
ሰኔ 24/2018 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው መስሪያ ቤቶች የተገኘባቸውን የኦዲት ከፍተቶች በ10 የስራ ቀናት ውስጥ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ፡፡ የኦዲት መረጃዎችን ማየት የፈለገ ማንኛውም አካል ደግሞ የኦዲት አድራጊ መስሪያ ቤቶችን ኃላፊዎች ፍቃድ ማግኘት ግዴታ አለበት ይላል መመሪያው፡፡ የመንግስት ንብረት ኦዲት መመሪያ ቁጥር190/2018 ኦዲት ተደራጊ መስሪያ ቤት ሥራ አመራርና የህንፃና ንብረት ሰራተኞች ኃላፊነታቸውን በብቃት መወጣታቸውን ለመረዳት ያስችላል ተብሏል፡፡ በተጨማሪም ንብረቶች ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን እና በስራ ላይ ባለ የህንፃና ንብረት አስተዳደር ሕጎች መሠረት ሥራዎች መከናወናቸውን ማረጋገጥ እና በኦዲት ግኝቱ መሠረት ኦዲት ተደራጊ መሥሪያ ቤቶች የእርምት እርምጃ መውሰዳቸውን መ
7 hours ago


በኢትዮጵያ ሰዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው የተሻለ ህክምናም ሲያስፈልጋቸው ምን ማድረጋቸው ይጠበቅባቸዋል ?
የሰኔ 24/2018 ሰው ጤናው ሲጓደል ለፈውስም መፍትሄ ሲፈልግ መካሪው ብዙ ሆኖ ይታያል፡፡ ሰዎች አንዳች የጤና ክልል ሲገጥማቸው፣ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሐሳብ ሲገባቸው የሚያግዛቸውን ፣ የተሻለ ህክምና አገልግሎትም ሲያሻቸው የሚጠቁማቸውንና የሚያማክራቸውን የጤና ማማከር አገልግሎትን ምርጫቸው ማድረግ በተለይ በውጩው አለም የተለመደ ነው ይባላል። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ሰዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው የተሻለ ህክምናም ሲያስፈልጋቸው ምን ማድረጋቸው ይጠበቅባቸዋል ? የጌትዌል ሜዲካል ትራቭል መስራች እና ስራ አስኪያጅ የሆኑትን ዶ/ር በጋሻው ባይለየኝን ጠይቀናል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….. ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡ https://www.shegerfm.com/ YouTube : https://shorturl.at
11 hours ago


ለሴቶችና ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር ኑሯቸውን ለማሻሻል ሲተገበር የቆየው የሊዌ ፕሮጀክት የስራ ፈጣሪዎችን አቅም አሻሽሎታል ተባለ፡፡
የሰኔ 24/2018 ለሴቶችና ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር ኑሯቸውን ለማሻሻል በኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት ድጋፍ ሲተገበር የቆየው የሊዌ ፕሮጀክት የስራ ፈጣሪዎችን አቅም አሻሽሎታል ተባለ፡፡ የኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት (SNV) ከመርሲ ኮርፕስ (Mercy Corps) ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ ሲተገብር የቆየው የሴቶች እና ወጣቶች የኑሮ ማሻሻያ (LIWAY) ፕሮግራም ተመዝግበዋል የተባሉ ለውጦችን የታዩበት ዝግጅት በትናንትናው እለት ተካሂዷል፡፡ ፕሮጀክቱ ለስራ ፈጣሪዎች ማስያዣ ሳይጠየቁ ከባነኮች ብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ፈጥሯል አንዲሁም መቀጠር ለሚፍሉጉ ድግሞ የቅም ግንባታ ስልጠና እንዲያገኙ ተድረጓል ሲሉ የፕሮጀክቱ ሃላፊ ሄለን ጌታቸው አስረድተዋል፡፡ በዚህም ላለፉት 4 ዓመታት 402,000 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወጣቶችና ሴቶችን የራሳቸው
11 hours ago


ግብር ከፋይዩና ሰብሳቢው ሳይግባቡ ሲቀር የጠ/ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚሰይመው ገለልተኛ አካል መፍትሔ እንዲሰጥ የሚፈቅድአዋጅ ጸደቀ፡፡
ሰኔ 23/2018 በግብር ከፋይዩ እና ሰብሳቢው መካከል አለመግባባት ሲፈጠር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚሰይመው ገለልተኛ አካል መፍትሔ እንዲሰጥ የሚፈቅደው የፌደራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ፡፡ ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2018 ፓርላማው ባከሄደው መደበኛ ሰብሰባ ያጸደቀው አዋጁ ታክስ ከፋዩ በታክስ እዳው ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል አዲስ ማስረጃ ካቀረበ አስቀድሞ ባለማቅረቡ ምክንያት ሊከፈል ይገባ የነበረውን የታክስ ዕዳ 10 በመቶ ቅጣት እንዲሚከፍል የሚያዝ ድንጋጌ ይዟል፡፡ አዋጁ በግብር ከፋይዩ እና ሰብሳቢው መካከል አለመግባባት ሲፈጠር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሚሰይመው ገለልተኛ አካል መፍትሔ እንዲሰጥ የሚያዝ ነው ፡፡ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ በታክስ ከፋዩ የሚቀርብ አዲስ ሰነድ፤ መረጃ፤ ማስረጃ ወይም
1 day ago


ከፍተኛ የት/ት ተቋማት በ4መመዘኛዎች 60 ከመቶ በላይ ውጤት ካመጡ ወደ ራስ ገዝነት ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያዝዝ መመሪያ
ሰኔ 23/2018 ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአራት መመዘኛዎች ከ60 ከመቶ በላይ ውጤት ካመጡ ወደ ራስ ገዝነት ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያዝዝ መመሪያ አወጣ። መመሪያው ዩኒቨርስቲዎች ራስ ገዝ ለመሆን በውስጣቸው የያዙትን የመምህራን የትምህርት ደረጃ መስፈርት የሚያደርግ ነው። ትምህርት ተቋማቱ በአስተዳዳር፣ በፋይናንስ፣ በሰው ኃይል አደረጃጀትና በአካዳሚክ አምዶች በተዘጋጀው መመዘኛ መሰረት ከ60 በመቶ በላይ ውጤት ካመጡ ወደ ራስ ገዝነት ሽግግር እንዲጀምሩ የትምህርት ሚኒስቴር ይፈቅዳል። መመሪያው የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ማሟላት የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች እና መመዘኛዎች ለመወሰን የወጣ ነው። በዚህም መሰረት የአስተዳደር አምድ 30 ከመቶ፣ ፋይናንስ 20 ከመቶ፣ ሰው ሃይል 15 እና አካዳሚክ አምድ 35 ከመ
2 days ago


ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡
ሰኔ 22/2018 ዘንድሮ በአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች 66 በመቶዎቹ ተማሪዎቻቸው ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል፡፡ የከተማዋ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መግለጫ ከመንግስት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች 95 ነጥብ 8 በመቶ፤ ከግል ት/ቤት ተማሪዎች ደግሞ ከ99 በመቶ በላዩ ማለፋቸውን ተናግሯል፡፡ የማለፊያ ነጥቡ 50 በመቶና ከዚያ በላይ ሲሆን 1 ሺህ 313 ተማሪዎች ከ90 በመቶ በላይ አግኝተዋል፡፡ በትምህርት ቢሮ ማህበራዊ ትስስር ገፅ የተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ ተማሪዎች ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ...... ፋሲካ ሙሉወርቅ
2 days ago
ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ያለባትን እዳ ለማሸጋሸግ ከአበዳሪዎቹ ጋር ስምምነት ላይ መድረሷ ተነግሯል፡፡
ሰኔ 22/2018 ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ያለባትን እዳ ለማሸጋሸግ ከአበዳሪዎቹ ጋር ስምምነት ላይ መድረሷ ተነግሯል፡፡ የ1 ቢሊዮን ዶላር እዳዋን ለማሸጋሸግ ከአበዳሪዎቹ ጋር ያደረገችው ተደጋጋሚ ድርድር ውጤት ሳያመጣ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ እንዲያውም አበዳሪዎቹ ጉዳዩን ወደ ህግ እንወስደዋለን እያሉም እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከሰኔ አምስት እስከ 28 ቀን 2026 በተደረገው ዝግ ውይይት የእዳ ሽግሽግ ድርድሩ በመርህ ደረጃ የሰመረ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ከ2 አመት በፊት መክፈል ከነበረበት የ1 ቢሊዮን ዶላር እዳ ላይ አበዳሪዎቹ 12 በመቶውን ለመቀነስ ተስማምተዋል፡፡ በዚህም ዋናው እዳ ከ1 ቢሊዮን ዶላር ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ እንዲል ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በሌላ በኩል በፈረንጆቹ አቆ
2 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
Mekoya - ሱዳናዊው ሰላይ በኢትዮጵያ ላይ - በእሸቴ አሰፋ
28:44

Now Playing
ለመሆኑ በአንድ በግዙፍ ድርጅት አስተዳደር ምን መሳይ መልክ ሊኖረው ይገባል? #economy #business #finance
07:59

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - ከባል አካውንት ለአባት የተላለፈው 400 ሺህ ብር የማን ነው?
04:12

Now Playing
የአሜሪካና ኢራን አዲሱ ውዝግብ - ሰኔ 17/2018 @ShegerFM1021Radio #shegerfm #iranamericawar
07:15

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32
bottom of page

