top of page


ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው 9 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች ተማሪዎችን ፈትኖ ለመቀበል መዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡
ነሐሴ 13 2018 ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው 9 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች ተማሪዎችን ፈትኖ ለመቀበል መዘጋጀቱን የትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ ባለፈው አመት በ5 ልዩ አዳሪ ትምህርትቤቶች 1ሺ 250 ተማሪዎች ተቀብሎ እያስተማረ እንደነበር የጠቀሰው ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ 4 ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ ብሏል፡፡ ባህር ዳር ፣ አርባ ምንጭ ፣ ድሬዳዋ እና አሶሳ አዳዲስ ልዩ ኣዳሪ ትምህርትቤቶች ሲሆኑ ቡኢ ፣ ወሊሶ ፣ጅግጅጋ ፣ ጋምቤላ እና ቦንጋ ደግሞ ነባሮቹ የፌደራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ናቸው፡፡ ዘንድሮ ወደ ፌደራል ልዩ አዳሪ ትምህርትቤት ለመወዳደር የ8ተኛ ክፍል ውጤታቸው 80 ከመቶና ከዛ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ኬጥኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመወዳደር ብቁ ናቸው ተብሏል፡፡ ከጠረፍ እና
14 minutes ago


የክልሎች ህገ መንግስት በክልሉ ያሉ ሁሉንም ብሔሮችን በሚጠብቅ መልኩ እንዲሻሻል እና "ልዩ ሃይል" አፍርሰናል ያሉ ክልሎች በገለልተኛ አካል ኦዲት እንዲደረጉ በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን ያለ ልዩነት መስማማቱ ተነገረ።
ነሐሴ 13 2018 የክልሎች ህገ መንግስት በክልሉ ያሉ ሁሉንም ብሔሮችን በሚጠብቅ መልኩ እንዲሻሻል እና "ልዩ ሃይል" አፍርሰናል ያሉ ክልሎች በገለልተኛ አካል ኦዲት እንዲደረጉ በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን ያለ ልዩነት መስማማቱ ተነገረ። በተቋማት ግንባታ ስር ሲመክር የቆየው ቡድን "ልዩ ሃይል" አንዲፈርስ ፣የክልል ፖሊስም በአገር አቀፍ ደረጃ ወጥ ሆኖ በሚዘጋጅ የስልጣን ሰነድ እንዲሰለጥን ከስምምነት መድረሳቸውን ሸገር ከቡድኑ አባላት ሰምቷል። ክልሎች የሚኖሯቸው የሚሊሻ አባላትም በወታደራዊ ሳይንስ የሰለጠኑ ይሁኑ በሚለው መመሪያ ላይ የተስማማው ቡድኑ አንድም የክልል የጸጥታ አደረጃጀት የመከላከያ እና ፌደራል ፖሊስን የሚገዳደር ሃይል እንዳይኖረው በሚለው መስማማታቸውን ተመካካሪዎች ነግረውናል ። ተመካካሪው ብድን ክልሎች አፍርሰናል ያሉት
2 hours ago
አስፈጻሚው የመንግስት አካል በግለሰቦች ላይ በደል ሲፈፅም የሚቀጣበት የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ስራ ላይ ቢሆንም ብዙዎች ነገሬ ብለው እንደማይጠቀሙበት በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ የህግ ባለሙያዎች ነግረውናል፡፡
ነሐሴ 13 2018 አስፈጻሚው የመንግስት አካል በግለሰቦች ላይ በደል ሲፈፅም የሚቀጣበት የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ስራ ላይ ቢሆንም ብዙዎች ነገሬ ብለው እንደማይጠቀሙበት በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ የህግ ባለሙያዎች ነግረውናል፡፡ አዋጁን የማስፈፀም ስልጣን የተሰጠው የፍትህ ሚኒስቴር ይህንን ጉዳይ ለመዳኘት በፌድራል ፍርድ ቤት የአስተዳደር ጉዳይ ችሎት ቢደራጅም በቂ አለመሆኑን ነግሮናል፡፡ የመንግስት ተቋማት የግለሰቦች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም የመከልከል፤ያለአግባብ ከስራ ማባረርና መሰል አስተዳደራዊ በደል ሲፈፅሙ ግለሰቡ የመንግስትን አካል ህግ ፊት አቁሞ መብቱን ማስከበር የሚያስችለው ይህ አዋጅ ስራ ላይ ከዋለ 6 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ በአዋጁ መሰረት አንድ በደል ደርሶብኛል የሚል ግለሰብ በመጀመሪያ በደል ባደረሰበት ተቋም ውስጥ ላለ ቅሬታ ሰሚ ክፍል
2 hours ago
ተማሪዎች የሰው ሠራሽ አስተውህሎት (AI) አጠቃቀም ላይ ከመምህራኖቻቸው ቀድመው የሚገኙ ከሆነ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ ክፍተት መፍጠሩ አንደማይቀር ተጠቆመ።
ነሐሴ 12 2018 ተማሪዎች የሰው ሠራሽ አስተውህሎት (AI) አጠቃቀም ላይ ከመምህራኖቻቸው ቀድመው የሚገኙ ከሆነ በመማር ማስተማር ሂደት ላይ ክፍተት መፍጠሩ አንደማይቀር ተጠቆመ። ችግሩን ለመቅረፍ መምህራንን በቴክኖሎጂው ማብቃትና AIን በራሱ እንደ አንድ የትምህርት ኮርስ አዋህዶ መስጠት እንደሚያስፈልግ የዘርፉ ተመራማሪዎች አሳስበዋል። ሰው ሰራሽ አስተውህሎት እያሳየ ባለው እድገት ምክንያት ከጊዜ በኋላ መምህራንን ሊተካ ይችላል የሚል ስጋትን ደቅኗል ተባለ፡፡ በኮተቤ የትምህርት ዩንቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አበበ አለሙ መምህራኑ በአግባቡ ለዚህ ቴክኖሎጂ ማዘጋጀት ከተቻለ ጊዜያቸውን እንዲጠቀሙ ተማሪዎቻቸውንም እንዲያበቁ ይረዳቸዋል ይላሉ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ቴክኖሎጂው እየሄደበት ባለው ፍጥነት ያልበቃውን መምህር ሊተካ ይችላል ፣ ተማሪዎች
20 hours ago


ጉዳት ከመድረሱ በፊት መቆጣጠር የተቻለውና ጉዳት መድረሱ በኦዲት የተረጋገጠ በአጠቃላይ 560 ቢሊየን 606 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገቦች ተደራጅተው ምርመራ ተጣርቶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ተናገረ።
ነሐሴ 12 2018 ጉዳት ከመድረሱ በፊት መቆጣጠር የተቻለውና ጉዳት መድረሱ በኦዲት የተረጋገጠ በአጠቃላይ 560 ቢሊየን 606 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገቦች ተደራጅተው ምርመራ ተጣርቶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ተናገረ። ከ2012 ጀምሮ በተከታታይ ለ6 አመታት በተካሄዱ የፋይናንስ፣ የሙስና፣ የታክስና ጉምሩክ፣ የኮንትሮባንድ፣ የባንክ ማጭበርበር ፣ ሕገ-ወጥ የሐዋላና የመሬት ወረራ ወንጀሎች ምርመራ ከፍተኛ የሀገር ሀብት ከጉዳት አትርፈናል ብሏል ተቋሙ፡፡ ተደራጅተው በተፈጸሙና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ አደጋ በደቀኑ ወንጀሎች ላይ በተደረገ የተቀናጀ ምርመራ፣ በአጠቃላይ 560 ቢሊዮን 606 ሚሊዮን 987 ሺህ 502 ብር የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገብ ተደራጅቶ መጣራቱን ጠቅሷል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከ2012 እስከ 2018
24 hours ago












bottom of page
_edited.jpg)








