top of page
ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ።
ሚያዝያ 24/2018 ዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ ከደንበኞቼ በአደራ መልክ የሰበሰብኩትን 16.9 ሚሊየን ብር ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ አደረግሁ አለ። 30ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ባንኩ ባዘጋጀው ዳሸን ኤክስፖ የማጠናቀቂያ መርሐ ግብር፤ የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ሸሪክ የ8 ዓመት የስኬት ጉዞን አስመልክቶ ማብራሪያ ተሰጥቷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ቺፍ ኦፊሰር አቶ አምዱ ሰማን ባንኩ ጠንካራ የሸሪዓ አማካሪ ኮሚቴ በማቋቋም የማህበረሰቡን ዕሴቶች ያከበሩና ሸሪዓውን የጠበቁ አገልግሎቶች መስጠቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት 'ሸሪክ' ከሚሰጣቸው ዘመናዊና አካታች የባንክ አገልግሎቶች ባሻገር ማህበራዊ ሐላፊ
1 day ago


ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡
ሚያዝያ 24/2018 ዘንድሮ 34 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተናገረ፡፡ ከ500 በላይ የመንገድ ፕሮጀክሮችን እየሰራ መሆኑን የሚጠቅሰው አስተዳደሩ ከግማሽ በላዩ እየተሰሩ ያለው በሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች ነው ብሎናል፡፡ አንዱና አካባቢ ከሌላው ገጠሩን ከከተማው የሚያገኛኙ የመንገድ ግንባታዎች፣ ጥገናዎችና የዲዛይን ስራዎች እየተሰራባቸው ያሉ ከ500 በላይ ፕሮጀክቶች እንዳሉ የነገሩን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሃመድ አብዱራህማን፣ ከእነዚህ መካከል የፈጣን መንገዶችን፣ ክልሎችን እርስ በስርስ የሚያገናኙ፣ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ተነስተው በ5 አቅጣጫ የሚወጡ ፕሮጀክቶች ናቸው ብለውናል፡፡ ለመሆኑ የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን ምን ያህል ደርሷል?ያልናቸው ሃላፊው ከ24ዓ
1 day ago


ስራ ፈጣሪዎች የሚያግዝ ፕሮግራም ይዞ መምጣቱን ክሪኤቲቭ ኪንግደም ተናገረ።
ሚያዝያ 24/2018 በየዘርፉ የስራ ፈጠራ ኖሯቸው የፈጠሩትን ስራ ወደ ተግባር የሚለውጡበት ያጡ ስራ ፈጣሪዎች የሚያግዝ ፕሮግራም ይዞ መምጣቱን ክሪኤቲቭ ኪንግደም ተናገረ። የራሳቸው መሆኑ ታውቆላቸው በአእምሮአዊ ንብረት ያስመዘገቡ ስራ ፈጣሪዎች ጭምር ፈጠራቸውን በገንዘብ፣ በሀሳብ፣ በመስሪያ ቦታ በመሳሰሉት የሚደግፋቸው ያጡ ሰዎች በየቦታው አሉ። ይህንን ችግር ለመፍታት፣ ስራ ፈጣሪዎች የሚታገዙበት ክሬቲቭ ኪንግደም የተባለ ፕሮግራሙን ስራ መጀመሩን ሰምተናል። ፕሮግራሙ ስራ ፈጣሪዎች ፈጠራቸውን ወደ ተግባር እንዲለብጡ፣ ህብረተሰቡም ለስራ ፈጣሪዎቹ ዋጋ እንዲሰጥ ያስችላል ሲሉ የክሪኤቲብ ኪንግደም ዋና ስራ አስፈጻሚ ታደሰ ኃይሉ ነግረውናል። ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ማርታ በቀለ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Website፡...
1 day ago


በኢትዮጵያ የአሉሚኒየም ምርቶች ላይ የተሰማራው ''ቴክሃፍ አሉሚኒየም'' አለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶችን በማሟላት እውቅና ማግኘቱ ተነገረ
ሚያዝያ 22/2018 በኢትዮጵያ ለአውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የሃይል ማመንጫዎች፣ኢንደስትሪ ፓርኮችና ሌሎችም ግዙፍ የግንባታ ስራዎች የሚውሉ የአሉሚኒየም ምርቶች ላይ የተሰማራው ቴክሃፍ አሉሚኒየም የተባለ ተቋም አለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶችን በማሟላት እውቅና ማግኘቱ ተነገረ፡፡ ተቋሙ በቅርቡ ወደ አለም አቀፍ ገበያ እንደሚቀላቀለም ጠቅሷል፡፡ ቴክሃፍ አሉሚኒየም አራት ዓለም አቀፍ የጥራት ምስክር ወረቀቶችን ማግኘቱ የተነገረ ሲሆን እውቅናዎቹ በኢትዮጵያ የተሰሩ ምርቶች በዓለማቀፍ ገበያ ገብተው እንዲወዳደሩ ለማድረግ በር የሚከፍት ነው ተብሏል፡፡ በዓለም ላይ የአሉሚኒም ምርቱ ካለው የምርት እድገት አንጻር የኢትዮጵያ ዝቅተኛ መሆኑን የሚያነሱት የቴክሃፍ አሉሚኒየም የሽያጭ ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ ጌታሁን ጥላሁን ተቋማቸው ይህንን ክፍተት ለማጥበብና የኢትዮጵያ
3 days ago


ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ ለመራጭነት ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ከእቅዱ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ተናገረ፡፡ አካል ጉዳተኞች አጠቃላይ ከማህበረሰቡ ከ17 በመቶ በላይ መሆናቸው ይነገራል፡፡ ከመካከላቸው 5 ሚሊየኑ የምርጫ ካርድ ይወስዳሉ ተብሎ ቢጠበቅም የወሰዱት ግን 167,000 ብቻ ናቸው ሲል ፌዴሬሽኑ ነግሮናል። የምርጫ ካርድ የወሰዱ አካል ጉዳተኞች ቁጥር ዝቅተኛ የሆነበት የመረጃ ክፍተት ምክንያት አንዱ እንደሆነም ተነግሯል። ይህን የነገሩን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ አብዛኛው አካል ጉዳተኛ የምርጫ ካርድ አለመውሰድ ጋር በተያያዘ ቅሬታችንን ለምርጫ ቦርድ አቅርበናል፤ እንደ ሃሳብ ያቀረብነውም የመራጮች ምዝገባ እንዲራዘም የሚል ነበር
3 days ago


አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 አቢሲንያ ባንክ ˝እችላለሁ˝ 5ኛ ዙር የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና የሎተሪ እድለኛን ለመለየት የእጣ ማውጠት ስነ ስርዓት አከናወነ፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት መድረክ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ የኩፖን ቁጥሮችን መሠረት በማድረግ የ2025 BYD Seagull ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና ዕድለኛን ለመለየት የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (March 8) በማስመልከት፣ “እችላለሁ ” በሚል መሪ ቃል ለ5ኛ ጊዜ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚያጎለብት መርሐ-ግብር ማካሄዱ ይታወሳል፡፡ ባንኩ ባሰናዳው መርሀ ግብር ላይም በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት ለመቀነስ፣ ሀገር አቀፍ የደም ልገሳ ዘመቻ ያከናወነ ሲሆን በዚህም 3,012 ዩኒት ደም መሰብሰብ
3 days ago
የፌድራል መንግስት በመንፈቅ ዓመቱ 93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስቴር ያውጣው የግማሽ ዓመት ሪፖርት አሳየ፡፡
ሚያዝያ 22/2018 የፌድራል መንግስት በመንፈቅ ዓመቱ 93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስቴር ያውጣው የግማሽ ዓመት ሪፖርት አሳየ፡፡ በሌላ በኩል የዘንድሮ የንግድ ሚዛን ልዩነት 6.2 ቢሊዮን ዶላር መሆኑም ተጠቅሷል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው ዘርዘር ያለና የበጀት አጠቃቀምን በሚያሳየው ሪፖርቱ ባለፉት 6 ወራት ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ምንጮች የተሰበሰበው ገቢ እንዲሁም አጋር ከተባሉ አካላት የተገኘውን ጨምሮ አጠቃላይ ገቢው 704.7 ቢሊዮን ብር መሆኑን ይጠቅሳል፡፡ ይሁንና በዚሁ ጊዜ ለመደበኛ፣ ለካፒታል ወጪዎችና ለክልሎች የተሰጠው የበጀት ድጎማ ተዳምሮ ወጪውን 798.2 ቢሊዮን ብር አድርሶታል፡፡ በዚህም ወጪውና ገቢው ባለመመጣጠኑ የ93.3 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንደገጠመ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ የገጠመው የበጀት
3 days ago


በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡
ሚያዝያ 21/2018 በ"ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ዓቃቢ ህግ ክስ እንዲመሰርት 7 ቀናት ተፈቀደለት፡፡ በፊንቴክ ኢንቨስትመንትሽፋን በተፈጸመ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮችን ጉዳይ ለመመልከት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለ ዓቃቢ ህግ ክስ መመስረቻ 7 ቀን የፈቀደው፡፡ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፖሊስ የምርመራ ስራዎችን አጠናቆ አንዲያቀርብ ነበር፡፡ በዛሬው ችሎትም ፖሊስ ምርመራውን መጨረሱንና ጉዳዩን ለዓቃቢ ህግ ማስተላለፉን አስረድቷል፡፡ ዓቃቢ ህግም ክስ ለመመስራት ፍርድ ቤቱን 10 ቀናት ጥይቆ 7 ቀናት ተፈቅዶለታል፡፡ በዚህም ለሚያዚያ 28/2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የፊንቴ
4 days ago
አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ።
ሚያዝያ 21/2018 አዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ለሚያስገቡ ደንበኞች የሁለት አመት የክፍያ ስርዓት ማመቻቸቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ። በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለአዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ የሚያስፈልገውን ክፍያ ከፍለው አገልግሎት ማግኘት ላልቻሉ ደንበኞች የተዘረጋው ይህ አሰራር እስከ 2 ዓመት በሚደርስ የክፍያ ስርዓት እንዲከፍሉ የሚያደርግ ነው ተብሎለታል። ተቋሙ ወደ ስራ ያስገባውን አዲስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን የሚችሉትም የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች ናቸው የተባለ ሲሆን የመኖሪያ ቤት እና አነስተኛ ንግድ ቤቶችን ያጠቃልላል ተብሏል። ይህንን አሰራር የጀመርኩት ጥናትን መሰረት አድርጌ ነው ያለው አገልግሎቱ በርካታ ደንበኞቼ በገንዘብ እጥረት ምክንያት አዲስ ቆጣሪ ማስገባት መቸገራቸውን ጥናቱ አሳይቷል ብሏል። ደንበኛው የጊዜ ገደ
4 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
መዓዛ ብሩ ከዶ/ር ተካልኝ ወልደማርያም እና ዶ/ር ዮናስ አሽኔ ጋር የተደረገ ወግ - ሚያዝያ 18 / 2018
35:12

Now Playing
መቆያ - የሁለት አምባገነን መሪዎች ሀገር - ክፍል 2 በእሸቴ አሰፋ #shegerfm #mekoya
23:16

Now Playing
ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ መሥራች መቶ አለቃ ትዕዛዙ ኮሬ ጋር የተደረገ ጨዋታ 3ኛ ሳምንት ክፍል - 2
34:45

Now Playing
ከዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ መሥራች መቶ አለቃ ትዕዛዙ ኮሬ ጋር የተደረገ ጨዋታ 3ኛ ሳምንት ክፍል - 1
32:51

Now Playing
ትዝታ ዘ አራዳ - ዕውቁ ዲፕሎማት እና ምሁር መላኩ በያን (ዶ/ር)
27:10

Now Playing
እስራኤል እና አሜሪካ ጦርነት አቁመው ከኢራን ጋር የስምምነት ፊርማ የሚያኖሩት መቼ ይሆን #Mamuasha #ማሟሻ
10:52

Now Playing
በአዲስ አበባ የመንግስት ሰራተኞች ለአደጋ ቅነሳ በሚል ከደመወዛቸው የመቆረጡ ጉዳይ
05:21

Now Playing
አየርላንድ ኢምባሲ ሴንት ፓትሪክ ቀንን በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪዎች ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ጋር በመሆን ያካሄዱት ዝግጅት Saint Patrick’s Day!
48:15
bottom of page

