top of page


በእጅጉ ለመጥፋት የተጋለጠ በሚል ደረጃ የተመደበው ዋልያ
ሐምሌ 9/2018 ዓለም አቀፉ የተፈጥሮ ጥበቃ ህብረት ከኢትዮጵያ ብርቅዬ እንስሳት መካከል ዋልያን በእጅጉ ለመጥፋት የተጋለጠ በሚል ደረጃ መመደቡ አፋጣኝ የጥበቃ እርምጃ እንደሚያስፈልገው የሚያሳይ ነው ተባለ፡ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የዋልያዎች ብዛት ከዓመታት በፊት ከነበረው በግማሽ ቀንሶ 300 ያህል እንደሆነ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ተናግሯል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ንጋቱ ረጋሳ
7 hours ago


የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ተለይተው በተወሰኑ የትምህርት መስኮች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲያሰተምሩ መደረጉ
ሐምሌ 9/2018 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ተለይተው በተወሰኑ የትምህርት መስኮች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲያሰተምሩ መደረጉ ለውጥ ማምጣቱን ጥናት አሳይቷል፡፡ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት መጓደልን ለማስተካከል በዘርፉ የተለያዩ የለውጥ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተልዕኮ እና በትኩረት ተለይተው እንዲሰሩ ማድረግ ለትምህርት ጥራትና ለሀገር ኢኮኖሚ ወሳኝ ነው ተብሎ ታምኖበት ወደ ስራ መገባቱ ይታወሳል፡፡ በዚህ መሰረት ሶስት ዋና ዋና ተልዕኮ ተለይቶ መተግበራቸው የሚታወስ ሲሆን የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች አፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርስቲዎች እንዲሁም አጠቃላይ ዩኒቨርስቲዎች በሚል መለየታቸው ተነግሯል፡፡ እነዚህ ተልዕኮዎች አሁን ላይ ለውጥ እያመጡ ነው ሲሉ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉት በአንቦ ዩኒቨርሲቲ
7 hours ago


አንድሮሜዳ የግል ት/ቤት የትምህርት ክፍያ በእጥፍ መጨመሩ ጥያቄ አስነስቶበታል፡፡
ሐምሌ 9/2018 በአዲስ አበባ አንድሮሜዳ የተባለው የግል ትምህርት ቤት በእጥፍ የትምህርት ቤት ክፍያ መጨመሩ የህጋዊነት ጥያቄ አስነስቶበታል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አምና ባወጣው ደንብ መሰረት የግል ትምህርት ቤቶች ከ65 በመቶ በላይ ጭማሪ ማድረግ እነደማይችሉ ጭማሪዉም ለሶስት አመት እንዲያገለግል መደንገጉ ይታወሳል፡፡ የተጠቀሰው ትምህርት ቤት ግን አምና ካደረገው ጭማሪ ባለፍ ዘንድሮም 100 በመቶ ጭማሪ ማድረጉን ወላጆች ተናግረዋል፡፡ የወላጆችን ቅሬታ ተቀብለን ትምህርት ቤቱንም ጠይቀናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…. ገዛ ጌታሁን
8 hours ago


በኤአይ የሚሰሩ የፈጠራ ውጤቶች በኢትዮጵያ የህግ ከለላና ጥበቃ ያገኛሉ ወይ?
ሐምሌ 8/2018 የሰው ልጅ በተፈጥሮ ያለውን እምቅ የፈጠራ አቅም ተጠቅሞ የሚሰራቸው ልዩ ልዩ ውጤቶች አዕምሯዊ ንብረቶቹ ሆነው በህግ እንዲጠበቁለት ይደረጋል፡፡ ይህ የህግ ጥበቃ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ( #AI ) የሚሰሩ የፈጠራ ውጤቶችን ይመለከታል ወይ? በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚሰሩ የስራ ፈጠራዎች እንዳሉ ሁሉ የሌላን ሰው ስራ በ AI በመታገዝ እንደራሳቸው የፈጠራ ስራ የሚያቀርቡ እንዳሉ ሰምተናል፡፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም የሚሰሩ የፈጠራ ውጤቶች በኢትዮጵያ የህግ ከለላና ጥበቃ ያገኛሉ ወይ? ስንል ጠይቀናል፡፡ በመደወላብ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ውስጥ ረዳት ፕ/ሮ የሆኑት ዓለሙ ባልቻ በጉዳዩ ላይ ጥናት አድርገዋል፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚሰሩ የፈጠራ ውጤቶችን ከለላና ጥበቃ ምታደርግበት የህግ ማዕቀፍ የላትም ብ
9 hours ago


የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ የመጠባበቂያ ክምችት ከወራት በኋላ ወደ ስድስት ቢሊዮን ዶላር እንደሚጠጋ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት IMF ተናገረ፡፡
ሐምሌ 8/2018 የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ የመጠባበቂያ ክምችት ከወራት በኋላ ወደ ስድስት ቢሊዮን ዶላር እንደሚጠጋ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት IMF ተናገረ፡፡ ይህም ከሁለት ወራት በላይ የውጭ ሸመታዋን ለመከወን የሚያስችል ነው ብሏል፡፡ ኢትዮ ከተቋሙ ጋር የጀመረችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሲጠናቀቅ ለሶስት ወር ተኩል ሸመታ የሚበቃ መጠባበቂያ ክምችት እንዲኖራት ይጠበቃል ብሏል፡፡ ይሁንና ይህ ግብ እንዳይሳካ እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ስጋቶች መኖራቸውንም IMF በስጋትነት አንስቷል፡፡ ተቋሙ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከተጀመረ ወዲህ አምስተኛው ዙር ግምገማ አካሂዶ ሙሉ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ 132 ገፅ በያዘው ሪፖርቱ አጠቃላይ ስለ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ሁኔታና ስለተረጋገጡበት ስጋቶች በስፋት ተንትኗል፡፡ እስካሁን ጠንካራ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም መኖሩንና
1 day ago












bottom of page
_edited.jpg)
















