top of page
ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ።
ሰኔ 5/2018 የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ። ብፁዕ ካርናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ኃላፊነታቸውን ያስረከቡት በጡረታ ምክንያት እንደሆነ ቤተክርስቲያኗ አስታውቃለች፡፡ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ላቀረቡት ከሃላፊነት የመነሳት ጥያቄ፤ በዛሬው ዕለት መቀበላቸውን በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ይፋ መደረጉን በቤተክርስቲያኗ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል፡፡ የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ተተኪ በመሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ረዳት ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ሆነው ተሹ
4 hours ago


በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው ለኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ።
ሰኔ 5/2018 በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩ ባለሃብቶች ለዓመታት ሲያቀርቡት የነበረው የማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል መሬት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል ተባለ። በግብርና ሚኒስቴር ድጋፍ ለማስፋፊያ እና ለአዲስ ኢንቨስትመንት የሚውል ተጨማሪ 33,000 ሄክታር መሬት በተለያዩ ክልሎች መገኘቱ ተነግሯል፡፡ እስከ አሁን ልማቱ ሲካሄድ የቆየው በ12,000 ሄክታር መሬት እንደነበር ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ሠምተናል። በኢትዮጵያ አሁን ላይ 120 የሚሆኑ ባለሃብቶች በአበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው እንደሚገኙ ተነግሯል። እነዚህ ባለሃብቶች እየሰሩ ያሉት 12,000 ሄክታር መሬት ላይ እንደሆነ ከኢትዮጵያ አበባ ፤ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች እና ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎ
4 hours ago


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል
ሰኔ 5/2018 የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የነዳጅ እጥረቱ፤ በወርቅ መገኘት የነበረበትን ገቢ እያሳጣ መሆኑን ተናገረ፡፡ ባለፉት 2 ወራት ብቻ የነዳጅ አቅርቦት ችግር የወርቅ ምርትን በ30 በመቶ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል ብሏል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ፤ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩ ከባለፉት ወራት የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ችግሩ በማዕድን ዘርፉ ላይ ጥላውን እንዳጠላበት ተናግሯል። በሌላ በኩል ክልሉ በዘንድሮው 9 ወራት 6222.5 ኪ.ግ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉንም ሰምተናል። ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከ47 ኩንታል በላይ ወርቅ ገቢ እንዳደረገም ተነግሯል። በዚህም አጠቃላይ በማዕድን ዘርፉ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ሲል ቢሮው ነግሮናል። የክልሉ የማዕድን
5 hours ago


በየቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል የሚፈጠሩት መቃቃር፣ አለመተማመኖች እና ችግሮችን ለመፍታት
ሰኔ 5/2018 በየቤት ሰራተኞች እና በአሰሪዎች መካከል የሚኖርን አሰራር ህጋዊ ለማድረግ አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ይታወቃል። ደንቡ እየተዘጋጀ ያለው በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ሲሆን ከሁለቱም ወገን ሊፈጠር የሚችልን አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጥቃቶችን ለመከላከል ያስችላል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ይህንን ደንብ ማውጣት አንዱ መሰራት ያለበት ስራ ቢሆንም የቤት ሰራተኞች ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት እና አሰሪዎችም እነሱን ከመቅጠራቸው አስቀድሞ ስልጠና ቢወስዱ መልካም እንደሚሆን በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ አንድ ባለሙያ ያስረዳሉ፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሁለቱም ወገን ያለው መቃቃር፣ አለመተማመኖች እና ችግሮች ክፍተቶቹ እየሰፉ መጥተዋል ያሉት ባለሙያው ህጉን ወረቀት ላይ ከማስፈር ባለፈ የሞያ ልምድ፣ ሰራተኞች ካሰሪዎቻቸው ጋር ስለሚደርጉት ተግባ
5 hours ago


ከምስራቅ ወለጋ በአዲስ መልክ ተፈናቅለናል ያሉ ሰዎች በደብረ ብርሃን በከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡
ሰኔ 5/2018 ከምስራቅ ወለጋ በአዲስ መልክ ተፈናቅለናል ያሉ ሰዎች በደብረ ብርሃን በከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ የምስራቅ ወለጋ አደጋ ስጋት በበኩሉ አዲስ ከአካባቢው የተፈናቀለ የለም ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም ከተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በደብረብርሃን የመጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ከ5 ዓመት በላይ እንደሆናቸ እና ቁጥራቸ ከ26,000 በላይ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ እነዚህ ተፈናቃዮች በቻይና፣ በወይንሸት፣ እንዲሁም በባቄሎ የመጠለያ ካምፖች ይገኛሉ፡፡ አሁን ደግሞ ከ3,000 በላይ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ወደ ወይንሸት ካምፕ መምጣታቸውን ተከትሎ በብዙ መቸገራቸውን ከተፈናቃዮች ሰምተናል፡፡ አዳዲስ የገቡትን ተፈናቃዮች በምን ምክንያት ወደ ደብረብርሃን ሄዳችሁ ስንል ጠይቀናቸዋል፡፡ እነሱም በነበሩበት ምስራቅ ወለጋ አሁንም የጸጥታ ችግር እ
5 hours ago


በመጪው ዓመት የመንግስትን ገቢ ለማሳደግ ያግዝ ዘንድ ከታክስ ነፃ እና የግብር እፎይታ አሰራሮች ሊቀሩ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
ሰኔ 5/2018 በመጪው ዓመት የመንግስትን ገቢ ለማሳደግ ያግዝ ዘንድ ከታክስ ነፃ እና የግብር እፎይታ አሰራሮች ሊቀሩ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ከዚህ ቀደም ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ ተደርገው ወደ ሀገር ይገቡ የነበሩ እቃዎች ከመጪው በጀት ዓመት ጀምሮ ቅናሽ የጉምሩክ የቀረጥ ምጣኔ እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል፡፡ በዚህም 22.5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማው ያቀረበው ረቂቅ በጀት ያሳያል፡፡ በተጨማሪም የገቢ ግብር እፎይታ አሰራርን ቀሪ በማድረግ የግብር እፎታ ይሰጣቸው የነበሩ በቅናሽ ምጣኔ ግብር በማስከፈል ሌላ 22 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር እንደሚሰበሰብ በረቂቁ ሰፍሯል፡፡ ከዚህ ቀደም የሴቶችን ስራ ለማቃለል በሚል የልብስና የእቃ ማጠቢያ ማሽኖች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ከተፈቀዱ መካከል ነበሩ፡፡ በተጨማሪም የጤናና የግብር ዘር
8 hours ago


‘’መንግስት ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ በዜጎች ላይ ጫና ይፈጥራል’’
ሰኔ 4/2018 መንግስት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀምረው በጀት ዓመት፤ ከታክስ ገቢ ወደ 1.5 ትሪሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱ በዜጎች ላይ ጫና ይፈጥራል የሚል ትችት ከፓርላማ አባል ቀረበበት፡፡ ዛሬ ለፓርላማ የቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ረቂቅ 2 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ሲሆን ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩን መንግስት ከታክስ ለመሰብሰብ ማቀዱን ተናግሯል፡፡ ይህም መንግስት ባለፈው ዓመት ከታክስ ለመሰብሰብ አቅዶት የነበረውን በጀት በግማሽ ትሪሊዮን ብር ይበልጣል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት መንግስት ከታክስ ገቢ ለማግኘት አቅዶት የነበረው የገንዘብ መጠን 1 ትሪሊዮን ነበር፡፡ በበጀት ረቂቁ ላይ ሀሳባቸውን የሰጡት የፓርላማ አባሉ እና የኢዜማ ተወካይ አብርሃም በርታ (ዶ/ር) ከግብር ለመሰብሰብ የታቀደው የገንዘብ መጠን ከፍተኛ መሆኑን ተ
1 day ago


ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶች
ሰኔ 3 2018 ከተረፈ ምርቶች፣ አገልግሎቶቻቸውን ከጨረሱ ባትሪዎች አካባቢን የማይጎዱ ምርቶችን የሚሰሩትን ወጣቶችንና እነሱን የሚረዱ ተቋማት እንዲደገፉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጠየቀ፡፡ ከተረፈ ምርቶች የንፅህና መጠበቂያ፣ ከሰል የመሳሰሉ ምርቶች የሰሩ ወጣቶችም፤ ቆሻሻ ሀብት እየፈጠረላቸው እንደሆነ ነግረውናል፡፡ ወጣቶቹ ወደ ስራ ሲገቡ አስፈላጊውን የሞያና የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡ ገንዘብና ሞያዊ ድጋፍ ካደረጉት መካከል ሪችፎር ቼንጅ አንዱ ነው፡፡ ድርጅቱ በሃሳብ ደረጃ የነበሩ 33 ድርጅቶች ንግድ መጀመር እንዲችሉ የሞያ ስልጠና እና ለእያንዳንዳቸው የ200 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ተናግሯል፡፡ ወደ ሥራ ገብተው እራሳቸውን በሀሳብ እና በፋይናንስ በማሳደግ ላይ ለሚገኙ 8 ድርጅቶች ደግሞ 1.5 ሚሊዮን ብር
1 day ago


የፌዴራል መንግስት ለክልሎች የደለደለው የበጀት
ሰኔ 4/2018 የፌዴራል መንግስት ለክልሎች ከደለደለው የበጀት ድጋፍ ትንሹ ለአዲስ አበባ የተመደበው 74.5 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ከፍተኛው ደግሞ ለኦሮሚያ ክልል 179.3 ቢሊዮን ብር ሆኖ መደልደሉን ከረቂቅ በጀቱ ተመልክተናል፡፡ ለመጪው የ2019 በጀት ዓመት የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማው ካቀረበው ረቂቅ በጀት እንደተመለከትነው ለ12 ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የተመደበው አጠቃላይ የበጀት ድጋፍ 520.5 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ ከመካከሉ ሁለተኛው ትልቁ ድጋፍ ለአማራ ክልል የተያዘው 112.4 ቢሊዮን ብር ነው፡፡ ሶማሌ ክልል በሶስተኛ ደረጃ 51.9 ቢሊዮን ብር ለ2019 ዓ.ም በጀት ተደልድሎበታል፡፡ ለደቡብ ኢትዮጵያ 36.5 ቢሊዮን ፣ ለትግራይ 31.3 ቢሊዮን፣ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ 30.9 ቢሊዮን ፣ ለሲዳማ ክልል ደግሞ 20.9 ቢሊዮን ብር ተ
1 day ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32

Now Playing
ማሟሻ - የኔን መንግስት በመልካም ስላገለገለ ወዳጃችንን በኒሻናችን አክብረን ሾመን ሸልመነዋል #shegerfm #muamuasha
09:31

Now Playing
ስም አይቀበርም - ሠዓሊ ለማ ጉያ #Lemma_Guya
01:10:56

Now Playing
የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ከአንድ እቃ ላይ የሚያተርፉት ምን ያክል ነው?
06:50

Now Playing
መቆያ - ሙሀሙሽን የክፉ ልማድ ሰለባዎች - በእሸቴ አሰፋ
29:19
bottom of page

