top of page
የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡
ግንቦት 20/2018 የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡ ከሰኔ 24 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ተኛ ክፍል ፈተና ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅት ማጠናቀቁን በተለያዩ ጊዜያት መነገሩ ይታወሳል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በክልሉ ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል በኦንላይን መፈተን የሚችለው 76 በመቶ ብቻ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በቀሪ ጊዜ ይህንን ቁጥር ወደ 80 በመቶ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ቢሮው የጠቀሰ ሲሆን ዘንድሮ 24 በመቶ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን በወረቀት ለመፈተን እየተዘጋጀ መሆኑን ነግሮናል፡፡ ለፈተናው የሚያስፈልጉ የኮምፒዩተር እጥረት፣ የኢንተርኔት አለመሟላት እና ሌሎች ግብአቶች እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክል
12 minutes ago


የምግብ ችግር እያለባትም፤ ካመረተችው ግማሽ የሚጠጋውን የምትደፋዋ ኢትዮጵያ!
ግንቦት 20/2018 በኢትዮጵያ በየዓመቱ ገበሬው ከሚያመርተው ምርት ከ40 በመቶ በላዩ ከገበታ ሳይደርስ ባክኖ ይቀራል። በየዓመቱ ከሚመረት እንደ ሽንኩርትና ቲማቲም ያለው ቶሎ የሚበላሽ የግብርና ምርት ግማሽ ያክሉ ተበላሽቶ የሚደፋ እንደሆነ ይነገራል። አፍሪካ በዚህ መንገድ ገበሬዎቿ ቢያመርቱም 4 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ምርት ተበላሽቶ መልሳ ትደፋለች። ከዚህ ጀርባ ያለው ትልቁ ችግር የቀዝቃዛ ምርት ማጓጓዣና መስቀመጫ ሰንሰለት አለመኖር ነው ይባላል። ያደጉት ሀገሮች ከአጠቃላይ ምርታቸው የምርት ብክነትን ከ1 በመቶ በታች ማውረድ ችለዋል። ኢትዮጵያ ግን የምግብ ችግር ቢኖርባትም፤ ዛሬም ብዙ ስለማምረት ብትደክምም ካመረተችው ግማሽ ያክሉን እየደፋች ቀጥላለች። ታዲያ ምን ይበጃል? የቀዝቃዛ ምርት ሰንሰለትን ማስፋፋትስ ለምን ከባድ ሆነ? የዘርፉ ባለሙያዎች
5 hours ago


የቅድመ ምርጫ አውዱን እየገመገመ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲፈቱ ከምርጫ ቦርድ እና ከሚመለከታቸው ጋር ለመነጋገር ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ድርጀቶች ህብረት ተናገረ፡፡
ግንቦት 18/2018 የቅድመ ምርጫ አውዱን እየገመገመ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲፈቱ ከምርጫ ቦርድ እና ከሚመለከታቸው ጋር ለመነጋገር ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ድርጀቶች ህብረት ተናገረ፡፡ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መንግስት ፣ ምርጫ ቦርድ ፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ ሚድያዎችና ሌሎችም የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....... https://l1nq.com/z0jzlsy ትዕግስት ዘሪሁን
2 days ago


“የድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠና” በኢትዮጵያ ቀዳሚው ነፃ የንግድ ቀጠና ነው።
ግንቦት 18/2018 “የድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠና” በኢትዮጵያ ቀዳሚው ነፃ የንግድ ቀጠና ነው። 2014 መጨረሻ ላይ ስራ የጀመረው ይህ ነፃ የንግድ ቀጠና ለጅቡቲ ወደብ በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የተቋቋመውና በኦሮሚያ ክልል ሞጆ ከተማ የሚገኘው ገዳ ነፃ የንግድ ቀጠና ደግሞ ሁለተኛው ነው፡፡ እነዚህ ነፃ የንግድ ቀጠናዎች በውስጣቸው መካሄድ በሚቻል ሰፋ ያሉ የኢኮኖሚ ተግባራት ከልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እንደሚለዩ ይጠቀሳል፡፡ በነጻ የንግድ ቀጠና ውስጥ ምርት ማምረት ፤ ንግድ ማካሄድ እና የሎጅስቲክስ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል፤በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ሃላፊ የሆኑት አቶ ጳውሎስ በለጠ ነግረውናል፡፡ የፋይናንስ እና ሆቴል አገልግሎቶችም ማቅረብ ይቻላል ብለዋል፡፡ ነጻየ
2 days ago


አሁን በስራ ላይ ያሉ ሁሉም አሽከርካሪዎች ሰልጥነው የብቃት ምዘና አንዲወስዱ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
ግንቦት 18/2018 አሁን በስራ ላይ ያሉ ሁሉም አሽከርካሪዎች ሰልጥነው የብቃት ምዘና አንዲወስዱ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡ ሁሉም አሽከርካሪዎች እንደገና እንዲሰለጥኑና እንዲመዘኑ በማድረግ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል አጠቃላይ የሰነድ ዝግጅት ተጠናቋል ያለው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ነው፡፡ ይህ አዲስ አሰራር ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ የምዘና ሂደቱ በዲጂታል ሲስተም እንዲመራ ተደርጎ ተቀርጿል ሲል ሚኒስቴር መ/ቤቱ መባህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መገለጫ ላይ ጠቅሷል ። አሽከርካሪዎች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ቅድሚያ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል ። በዚሁ መሰረት ይህንን ሀገራዊ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ትግበራ ለማስገባት በተለይም አጠቃላይ የአሽከርካሪዎች ምዝገባ እና ስ
2 days ago


የአፍሪካ ቀን
ግንቦት 18/2018 አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ የግጭትና የረሃብ ቀጠና ተደርጋ በመሳሏ ምክንያት ለኢንቨስትመት አመቺ ካልሆኑ አህጉራት መካከል በመሆኗ በየዓመቱ 4.2ቢሊዮን ዶላር እንደምታጣ ጥናት አሳየ፡፡ በየዓመቱ ግንቦት 17 የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 በዚህ ቀን መመስረቱን ተከትሎ የአፍሪካ ቀን ተብሎ ይከበራል። የዘንድሮውን የአፍሪካ ቀን Africa no filter የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት "አፍሪካ እየጠበቀች አይደለም"የሚል የሚዲያ ዘመቻ በማስጀመር 63ኛውን የአፍሪካ ቀን በትላንትናው እለት አክብሯል፡፡ አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ ለዘመናት የረሃብና የሰቆቃ ምልክት ተደርጋ ስትገለፅ ቆይታለች ያሉን የአፍሪካ ኖ ፊልተር ዋና ዳይሬክተር ሞኪ ማኩራ ናቸው፡፡ ድርጅታቸው
2 days ago


አንዳንድ ሆቴሎች ከመደበኛው ክፍያ በተጨማሪ የአገልግሎት በሚል የሚያስከፍሉት ክፍያ!
ግንቦት 18/2018 በአዲስ አበባ የምግብና መጠጥ አገልግሎት የሚሰጡ አንዳንድ ሆቴሎች ከመደበኛው ክፍያ በተጨማሪ የአገልግሎት እያሉ ሂሳብ ይቀበላሉ። በሌሎች ሀገራት ደንበኛው በተሰጠኝ አገልግሎት ተደስቻለሁ ካለ ብቻ በራሱ ፍቃድ የሚፈጽመው የአገልግሎት ክፍያ (ቲፕ)በእነዚህ ሆቴሎች አስገዳጅ ሆኖ እየተጠየቀ ነው። በዚህ መልክ የተሰበሰበውን ገንዘብ በመስተንግዶ ስራ ላይ ለተሰማሩ ሠራተኞቻቸው እንደሚያከፋፍሉትም የሆቴሎቹ ባለቤቶችና ሃላፊዎች ሲናገሩ ይሰማል። በርግጥ ግን የአገልግሎት ክፍያ ወይም ቲፕ በአስገዳጅነት ሊጠየቅ ይችላል? ሆቴሎቹ እንዳሉት ለአስተናጋጆቹ ስለ ማከፋፈላቸውስ እንዴት ይረጋገጣል? ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ…… ማርታ በቀለ
2 days ago


የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡
ግንቦት 17/2018 የመንግስት ግዥ አገልግሎት በዘንድሮው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች የተገኘ ወደ 323 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ አድርጌያለሁ አለ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያህል ገንዘብ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ለመንግስት ገቢ ሲያደርግ በታሪኩ የአሁኑ የጀመሪያው እንደሆነ ነግሮናል፡፡ የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌሎች ንብረቶች ከ322 ሚሊየን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ ማድረጉን ተናገረ፡፡ አገልግሎቱ የ90 መስሪያ ቤቶችን 271 ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ ለመንግስት ገቢ የሆነ ገንዘብ እንደሆነ ተጠቅሷ ። በሽያጭ ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች እና ሌ
3 days ago
ከአንድ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያዊያን በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በተለያዩ ስራዎች ተሰማርተው እንደሚገኙ ይነገራል።
ግንቦት 17/2018 የእቃ አስተላላፊነት ዘርፍን ለውጪ ባለሀብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት አንዲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ወሰነ፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ የእቃ አስተላላፊነት ዘርፍን ለውጭ ባለሃብቶች ተሳትፎ ክፍት ለማድረግ ውሳኔ ማሳለፉ ተሰምቷል፡፡ ቀደም ሲል የውጭ ባለሀብቶች የዕቃ አስተላላፊነት የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለአገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች የቅንጅት ኢንቨስትመንት የተከለለ ሲሆን የውጭ ባለሃብቶች የካፒታል የሽርክና ተሳትፎም በ49 በመቶ ተገድቦ መቆየቱ ተነስቷል። ከዚህም የተነሳ በዘርፉ የሚፈለገውን አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍሰት ላይ ክፍተት ፈጥሮ የቆየ ሲሆን የቦርዱ ውሳኔም ይህን እና መሰል ችግሮችን የሚቀርፍ እንደሚሆን ይጠበቃል ተብሏል፡፡ በዘርፉ የተሰማሩ ነባር ባለሃብ
3 days ago



Facebook
Twitter
Pinterest
Tumblr
Copy Link
Link Copied
Search video...

Now Playing
እንደ ቤተሰብ - ዛሬም በኢትዮጵያ 40 ሺህ ህፃናት ከዚህ ችግር ጋር ይወለዳሉ'
57:31

Now Playing
በሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
04:54

Now Playing
አልሰማንም እንዳትሉ - የፖለቲካ ሹም ሽር በፍርድ ቤት ይዳኛልን?
04:21

Now Playing
አሜሪካ ጫፌን የምትነካ ከሆነ ኬብሎቹን ቆርጬ የኢንተርኔት ስርዓቱን አስተጓጉላለው #shegerfm #iranisraelwar
07:32

Now Playing
ማሟሻ - የኔን መንግስት በመልካም ስላገለገለ ወዳጃችንን በኒሻናችን አክብረን ሾመን ሸልመነዋል #shegerfm #muamuasha
09:31

Now Playing
ስም አይቀበርም - ሠዓሊ ለማ ጉያ #Lemma_Guya
01:10:56

Now Playing
የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ከአንድ እቃ ላይ የሚያተርፉት ምን ያክል ነው?
06:50

Now Playing
መቆያ - ሙሀሙሽን የክፉ ልማድ ሰለባዎች - በእሸቴ አሰፋ
29:19
bottom of page

