top of page
ዋና ገጽ
ወሬ
መሰናዶዎች
የጊዜ ሰሌዳ
ከእኛ ጋር ያስተዋውቁ
ስለ እኛ
መገናኛችን
More
Use tab to navigate through the menu items.
የንግድ ህጉን ተላልፈው ተገኝተዋል ያላቸውን ከ24 ሺህ 500 በላይ ነጋዴዎች መቅጣቱን የንግድ ቢሮ ተናገረ።
ሐምሌ 21 2018 የንግድ ህጉን ተላልፈው ተገኝተዋል ያላቸውን ከ24 ሺህ 500 በላይ ነጋዴዎች መቅጣቱን የንግድ ቢሮ ተናገረ። ቢሮው የ2018 ዓ.ም የእቅድ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት የቢሮ ሃላፊዋ ወ/ሮ ሃቢባ ሲራጅ ነጋዴዎቹን ለቅጣት ያበቃቸው ያለ ንግድ ፈቃድ መነገድ፣ ባልታደሰና በተሰረዘ ንግድ ፈቃድ መነገድ ጭምር መሆኑን ተናግረዋል። የንግድ ህጉን አክብሮ ያለመስራት በዚህ ዓመትም ችግር ሆኖ ቀጥሏል የሚሉት ሃላፊዋ ከተቀጡት ነጋዴዎች አብዛኞቹ የፈጠሩትን ችግር እስከሚያስተካክሉ ድረስ የማሸግና ማስጠንቀቂያ የመስጠት ነው፤ በዚህም ከ24 ሺህ 500 በላዩ 90 በመቶዎቹ አስተካክለው ወደ ስራቸው ተመልሰዋል ብለዋል። ይሁንንና አሁንም ያለ ንግድ ፈቃድ መነገድ፣ ኪሎ ቀንሶ መሸጥ፣ ባዕድ ነገሮችን መቀላቀልና ሌልውም ችግር ሆኖ መቀጠሉንና በመጪው ዓመት
27 minutes ago
በኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት እንዲፈቀድ ለማድረግ እንደሚሟገቱ በሃገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ የዳያስፖራ ተወካዮች ተናገሩ፡፡
ሐምሌ 21 2018 በኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት እንዲፈቀድ ለማድረግ እንደሚሟገቱ በሃገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ የዳያስፖራ ተወካዮች ተናገሩ፡፡ አላግባባ ያሉና አንገብጋቢ ናቸው ተብለው በተመረጡ 8 አጀንዳዎች ላይ ሃገራዊ ምክክር መካሄድ ከጀመረ ቀናት ተቆጥረዋል፡፡ በምክክሩ ተሳታፊ ከሆኑ 4ሺህ ተመካካሪዎች 100 ያህሉ የዳያስፖራ ተወካዮች ናቸው፤ ከመካከላቸው ሁለቱን ምክክሩ ላይ ስላላቸው ተሳትፎ ጠይቀናቸዋል፡፡ በአባይ ጉዳይ ላይ በአረቢኛ ቋንቋ በግብፅ ሚዲያዎች የሚሰሩ ዘገባዎችን ወደ አማርኛ እየተረጎሙ በሚዲያቸው በማቅረብ የሚታወቁት ኡዝታዝ ከማል በሽር ተፅዕኖ ፈጣሪ ዳያስፖራዎችን በመወከል በምክክሩ እየተሳተፉ እንደሆነ ነግረውናል፡፡ በምክክሩ በአጀንዳነት ከተያዘው የሃገር ግንባታ ስር ካሉት ንዑሳን አጀንዳዎች አንዱ የዳያስፖራው አንገብጋቢ ጥያቄ የ
1 hour ago
ዓለም እንድትቀጥል አንዲት ሴት በሕይወት ዘመኗ 2.1 ልጅ እንድትወልድ ቢያስፈልግም፣ አሁን ያለው ግን 1.1 መሆኑን ጥናት አሳየ።
ሐምሌ 21 2018 ዓለም እንድትቀጥል አንዲት ሴት በሕይወት ዘመኗ 2.1 ልጅ እንድትወልድ ቢያስፈልግም፣ አሁን ያለው ግን 1.1 መሆኑን ጥናት አሳየ። የዓለም የሕዝብ ዕድገት ምጣኔ እያሽቆለቆለ መምጣቱን ያሳየውን ጥናት ያጠናው የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ተቋም ወይም UNFPA ነው። UNFPA የዓለም የሥነ ሕዝብ ቀንን በማስመልከት፣ ትዳር የመመሥረት፣ ልጅ የመውለድ የመሳሰሉ የወጣቶች ፍላጎቶችን በተመለከተ ያጠናውን ጥናት አዲስ አበባ ላይ ይፋ አድርጓል። ጥናቱ 73 አገሮችን እና ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 39 ዓመት የሆኑ 108 ሺህ ወጣቶችን በመጠየቅ እንደ ተጠናቀቀም ተነግሯል። የጥናቱ ውጤትም ዓለም እንድትቀጥል አንዲት ሴት በሕይወት ዘመኗ መውለድ ከሚጠበቅባት በግማሽ ያነሰ እየወለደች መሆኑን ማሳየቱን፣ በUNFPA የወጣቶች ተሟጋች ቤዛዊት እድሉ
1 hour ago
በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡
ሐምሌ 21 2018 በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡ ይህም ህፃናቱ ተወልደው በ90 ቀናት ውስጥ የተመዘገቡ ናቸው ሲሉ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮሴፍ ንጉሴ አስረድተዋል፡፡ ዘግይተው የልደት ምዝገባ ካደረጉት ጋር ተደምሮ በ2018 የሲቪል ምዝገባ አገልግሎት ያገኙ ህፃናት ቁጥር ግን 385 ሺህ መሆኑን ሰምተናል፡፡ እንዲሁም 40 ሺህ 668 የጋብቻ ምዝገባ ለማድረግ አቅዶ 37 ሺ 149 መመዝገቡን መቻሉንም ሰምተናል፡፡ በዚህም ጋብቻ በተደረገ በወቅቱ የተመዘገቡት 10 ሺህ 972 ናቸው ተብሏል፡፡ በበጀት አመቱ 9 ሺ 558 ፍቺ ለመመዝገብ ታቅዶ ከ13 ሺ በላይ መመዝገባቸው ተነግሯል፡፡ በወቅታዊ የፍቺ ምዝገባ ያደረጉት 4 ሺህ
2 hours ago
ከሃያ አመት በፊት በኢንቨስትመንት ስም ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ጉዳት እያስከተለ ባለው የማንጎ ዝርያ ላይ የትምህርት ተቋማት ምርምር እያካሄዱ ናቸው ተባለ።
ሐምሌ 21 2018 ከሃያ አመት በፊት በኢንቨስትመንት ስም ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ጉዳት እያስከተለ ባለው የማንጎ ዝርያ ላይ የትምህርት ተቋማት ምርምር እያካሄዱ ናቸው ተባለ። መነሻውን ጋምቤላ አካባቢ በነበሩ ጥቂት እርሻዎች ላይ አድርጎ የነበረው ዝርያው አሁን ላይ መላ ኢትዮጵያን ማዳረሱ ተጠቅሷል። ተክሉ በፍጥነት በመባዛት ነባሩን የማንንጎ ዝርያ እያጠፋ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ወንዳለ ሃብታሙ ነግረውናል። አሁን ላይ የምርምር ተቋማት ተክሉ የሚያመጣውን ችግር እንዴት ማስቀረት ይችላል በሚለው ላይ እየሰሩ ናቸው ብለውናል። በአማራ እና ትግራይ ክልሎች በሰፊው ይታወቅ የነበረው የበለስ ተክልም ከውጪ በገባ ኩችኔት በተባለ በሽታ እየተመናመነ እንደሚገኝ ተነግሯል። ሰዎች ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ የተሻለ ምርት
3 hours ago
1
2
3
4
5
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች
5 hours ago
የሐምሌ 20 የውጭ ሀገር ወሬዎች
1 day ago
የሐምሌ 17 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች
4 days ago
1/99
የንግድ ህጉን ተላልፈው ተገኝተዋል ያላቸውን ከ24 ሺህ 500 በላይ ነጋዴዎች መቅጣቱን የንግድ ቢሮ ተናገረ።
27 minutes ago
በኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት እንዲፈቀድ ለማድረግ እንደሚሟገቱ በሃገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ ያሉ የዳያስፖራ ተወካዮች ተናገሩ፡፡
1 hour ago
ዓለም እንድትቀጥል አንዲት ሴት በሕይወት ዘመኗ 2.1 ልጅ እንድትወልድ ቢያስፈልግም፣ አሁን ያለው ግን 1.1 መሆኑን ጥናት አሳየ።
1 hour ago
1/1375
በኢትዮጵያ በቆዳና ሌጦ ዘርፍ ሲሰሩ ከነበሩ 31 ፋብሪካዎች ውስጥ አሁን በስራ ላይ ያሉት ሰባት ብቻ ናቸው ተባለ።
5 days ago
በኢትዮጵያ የጭነት ማስተላለፍ ስራ ለውጭ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ክፍት እንዲሆን ተወስኗል።
Jul 1
የሜትር ታክሲ አገልግሎት አቅራቢው ''ያንጎ'' ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ ሥራ በመጀመሩ ተሰማ።
Jun 8
1/90
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Play Video
Load More
bottom of page