top of page


ጉዳት ከመድረሱ በፊት መቆጣጠር የተቻለውና ጉዳት መድረሱ በኦዲት የተረጋገጠ በአጠቃላይ 560 ቢሊየን 606 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገቦች ተደራጅተው ምርመራ ተጣርቶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ተናገረ።
ነሐሴ 12 2018 ጉዳት ከመድረሱ በፊት መቆጣጠር የተቻለውና ጉዳት መድረሱ በኦዲት የተረጋገጠ በአጠቃላይ 560 ቢሊየን 606 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገቦች ተደራጅተው ምርመራ ተጣርቶባቸዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ተናገረ። ከ2012 ጀምሮ በተከታታይ ለ6 አመታት በተካሄዱ የፋይናንስ፣ የሙስና፣ የታክስና ጉምሩክ፣ የኮንትሮባንድ፣ የባንክ ማጭበርበር ፣ ሕገ-ወጥ የሐዋላና የመሬት ወረራ ወንጀሎች ምርመራ ከፍተኛ የሀገር ሀብት ከጉዳት አትርፈናል ብሏል ተቋሙ፡፡ ተደራጅተው በተፈጸሙና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ አደጋ በደቀኑ ወንጀሎች ላይ በተደረገ የተቀናጀ ምርመራ፣ በአጠቃላይ 560 ቢሊዮን 606 ሚሊዮን 987 ሺህ 502 ብር የሚገመት የወንጀል ምርመራ መዝገብ ተደራጅቶ መጣራቱን ጠቅሷል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከ2012 እስከ 2018
2 hours ago
የነሐሴ 12 የውጪ ሀገር ወሬዎች
#ሩሲያ የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቭላድሚር ፑቲን ብሪታንያን በብርቱ አስጠነቀቋት፡፡ ፑቲን ብሪታንያ ለዩክሬይን ግዛት ተሻጋሪ ድሮኖችን ከማቀበል ብትቆጠቢ ይሻልሻል ማለታቸው ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ቀደም ሲል ታይምስ ጋዜጣ ዩክሬይን በሩሲያ ላይ ግዛት ተሻጋሪ ጥቃት የምታደርሰው በብሪታንያ ስሪት ድሮኖች እንደሆነ መዘገቡ ተጠቅሷል፡፡ ከቅርብ ወራት ወዲህ ዩክሬይን በሩሲያ ላይ ግዛት ተሻጋሪ የድሮን ጥቃቷን እየደጋመች መሆኑ ይነገራል፡፡ ፑቲን እና ሌሎች የሩሲያ ሹሞች ብሪታንያ ዩክሬይንን በተራቀቁ ድሮኖች ማስታጠቋ ውድ ዋጋ ያስከፍላታል ሲሉ መዛታቸው ተሰምቷል፡፡ ሩሲያ ከዩክሬይን ጋር ስትዋጋ ከ4 አመታት በላይ ሆኗታል፡፡ ዩክሬይን ድሮኖችን ለውጊያ ማዋሏ እየጨመረ መምጣቱ ይነገራል፡፡ #ሶማሊያ በሶማሊያ የባህር ዳርቻ አንድ የጭነት መርከብ በታጠቁ የባህር ወንበዴዎች
2 hours ago


በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
ነሐሴ 12 2018 በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል። በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሰምተናል። ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው
5 hours ago
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለም ዙሪያ ከኢነርጂ ደህንነትና ስብጥር ጋር የተገናኘ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል።
ነሐሴ 12 2018 የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለም ዙሪያ ከኢነርጂ ደህንነትና ስብጥር ጋር የተገናኘ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። እንዲህ አይነት ጦርነት በተነሳ ቁጥር የተቀረው አለም የነዳጅ አቅርቦት የሚስተጓጎል ከሆነ አለም አስተማማኝ የኢነርጂ ምርጫዋ ምን ቢሆን ይበጃል? የሚል ነው ጥያቄው። በሌላ በኩል ተፅዕኖው በደንብ ይታይ ከጀመረው የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተገናኘም እንደ ነዳጅና የድንጋይ ከሰል ያለው አካባቢን በካይ የኃይል ምንጭ በምን ቢተካ ይበጃል? ተብሎም እየተጠየቀ ነው። በብዙ ሀገሮች የቀጣዩ ዘመን አማራጭ የኃይል ምንጭ፣ከብክለትም ነፃ ተብሎ ግሪን ሃይድሮጂን (Green Hydrogen) መፍትሄ ተብሎ እየቀረበ ነው። ግሪን ሃይድሮጂን ታዳሽና ንፁህ የሆነ እንደ ነፋስ፣ ፀሐይና ከውሃ ኃይል ማመንጫ የሚገኝ ኤሌክትሪክን
5 hours ago


አቶ መስፍን ኤልዶ «85 ሺህ ብር ከባንክ ሒሳቤ የተወሰደብኝ ስልኬ በጠፋ በ4ኛው ቀን ነው» ይላሉ።
ነሐሴ 12 2018 አቶ መስፍን ኤልዶ «85 ሺህ ብር ከባንክ ሒሳቤ የተወሰደብኝ ስልኬ በጠፋ በ4ኛው ቀን ነው» ይላሉ። «ስልኬ ቅዳሜ ዕለት ተሰረቀ። ወዲያው ባንክ ሄጄ የባንክ ሒሳቤ እንዳይንቀሳቀስ አሳገድኩ፤ የባንክ ምስጢር ቁጥሬን ከእኔ ውጪ ማንም አያውቅም፤ የስልክ ቀፎዬ ላይም አልጻፍኩም። የባንክ ሒሳቤንም ያሳገድኩት እንደው ለምናልባቱ ብዬ እንጂ የባንክ ሒሳቤ ይመዘበርብኛል ብዬ አልነበረም» በማለት ያስረዳሉ። ቅዳሜ ዕለት ያሳገዱትን የባንክ ሒሳብ ሰኞ ዕለት ካስከፈቱ በኋላ በነገታው ማክሰኞ 85 ሺህ ብር ተወስዶባቸዋል። ሌላኛው ተጎጂ አቶ በለጠ ሙላት ደግሞ የስልክ ቀፎ ሳይሆን የሲም ካርድ ከተሰረቀባቸው በኋላ 120 ሺህ ብር ከሒሳብ አካውንታቸው እንደተዘረፈ ነግረውናል። «ከእኔ የወጣው ብር ወደ አራት ሰዎች የሒሳብ አካውንት እንደተዘዋወረ ባንኮ
5 hours ago












bottom of page
_edited.jpg)







