top of page

ህዳር 28፣ 2015ሩዋንዳ በምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣው M-23 አማፂ ቡድን የተነሳ ከአሜሪካ ጋር ክፉ ደግ እየተነጋገረች ነው ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • Dec 7, 2022
  • 1 min read

ህዳር 28፣ 2015


ሩዋንዳ በምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣው M-23 አማፂ ቡድን የተነሳ ከአሜሪካ ጋር ክፉ ደግ እየተነጋገረች ነው ተባለ፡፡


ኮንጎ ኪንሻሣ ጎረቤት ሩዋንዳ የአማፂው ቡድን አይዞህ ባይ ነች ስትል መቆየቷን አፍሪካ ኒውስ አስታውሷል፡፡


የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የኮንጎ ኪንሻሣን ክስ በማስተጋባት ሩዋንዳን M-23 ን መርዳትሽን አቁሚ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


ይሄን ተከትሎ የሩዋንዳ መንግስት የምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣውን የፀጥታ መደፍረስ በማባባስ ላይ ያለው አለም አቀፉ ማህበረሰብ ነው ማለቱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ሩዋንዳ በምስራቃዊው የኮንጎ ኪንሻሣ ግጭት እጄ የለበትም ስትል እንደምትምል እና እንደምትገዛት ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page