top of page

ህዳር 29፣ 2015- የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሳውዲ አረቢያ መግባታቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Dec 8, 2022
  • 1 min read

ህዳር 29፣ 2015


የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂን

ፒንግ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሳውዲ አረቢያ መግባታቸው ተሰማ፡፡


ሺ ጂን ፒንግ በሳውዲ ጉብኝታቸው ፈርጀ ብዙ ጉዳዮች እንደሚጠብቋቸው ሚድል ኢስት ሞኒተር ፅፏል፡፡


የቻይናው መሪ ከሳውዲ አረቢያ ሹሞች ጋር በበርካታ ጉዳዮች ከሚያደርጉት ንግግር በተጨማሪ ከባሕረ ሰላጤው በአጠቃላይም ከአረብ አገሮች መሪዎች ጋር እንደሚነጋገሩ ታውቋል፡፡


የሺ ጂን ፒንግ የሳውዲ አረቢያ ተልዕኮ በቻይና እና በአረብ አገሮች መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገምቷል፡፡


ከሁለቱም ወገኖች በኩል ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳለ ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page