top of page

ህዳር 4፣2017-መንግስት ለሽያጭ ለሚያቀርባቸው 900 ቢሊየን ብር የሚያወጣ የግምጃቤት ሰነድ ገንዘቡን ከየት አምጥቶ ይከፍላል?

  • sheger1021fm
  • Nov 14, 2024
  • 1 min read

ለመንግስት የልማት ድርጅቶች በሰጠውና ባልተመለሰለት ወደ 900 ቢሊዮን ብር የተጠጋ ብድር ምክንያት ሊፈርስ ነበር የተባለውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ለማትረፍ መንግስት እዳውን የሚመጥን የግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ ሊያቀርብ መሆኑ ታውቋል፡፡


የገንዘብ ሚኒስቴር የግምጃ ቤት ሰነዱን ለሚገዙት ተቋማት ገንዘቡን ከነወለዱ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡


ይህም ወጭውን ስለሚያንረው የበጀት ጉድለቱን እየለጠጠው እንደሚቀጥል የምጣኔ ሐብት ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡


በተጨማሪም መንግስት ገንዘቡን ለመክፈል የሚወስዳቸው ርምጃዎች የህዝብን ኑሮ ጫና ውስጥ ሊከቱ እንደሚችሉ ሰምተናል፡፡


የፖሊሲ ስህተት ትውድን ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍል ማሳያ ነውም ተብሏል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page