top of page

ህዳር 4፣2017 በእስራኤል የመከላከያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ከፍተኛ ሹም የነበሩት ኢያል ዛሚር ሀላፊነታቸው ለቀቁ

  • sheger1021fm
  • Nov 14, 2024
  • 1 min read

በእስራኤል የመከላከያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ከፍተኛ ሹም የነበሩት ኢያል ዛሚር ሀላፊነታቸው ለቀቁ፡፡


ከሳምንት በፊት የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር ዮአብ ጋላንት በጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ከኃላፊነት እንደተባረሩ ሚድል ኢስት ሞኒተር አስታውሷል፡፡


የኢያል ዛሚር ሀላፊነት መልቀቅም ከዮአብ ጋላንትን መባረር የተከተለ ነው ተብሏል፡፡


ይሁንና ዛሚር ሀላፊነታቸውን የለቀቁበት ምክንያት በዝርዝር አልተጠቀሰም ተብሏል፡፡


የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስቴር ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለመገናኛ ብዙሃን በማሾለክ ውዝግብ ሲታመስ መሰንበቱ ይነገራል፡፡


በሚስጥሩ ማፈትለክ የተነሳ በጦር ካቢኔው ውስጥ የሚደረግ ምክክር እንዳይቀረፅ መከልከሉ ተጠቅሷል፡፡


የኔነህ ከበደ

Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page