top of page

ሐምሌ 11፣ 2016 - የውጭ ሀገር ፓስፖርት ያላችሁ ሁሉ የሆቴል አገልግሎት የሚያገኙት በውጭ ምንዛሬ እንዲሆን የሚያዘው የቆየ መመሪያ ቁጥጥሩ ሊበረታ ይገባል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jul 18, 2024
  • 1 min read

የውጭ ሀገር ፓስፖርት ያላችሁ ሁሉ የሆቴል አገልግሎት የሚያገኙት በውጭ ምንዛሬ እንዲሆን የሚያዘው የቆየ መመሪያ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱን የሚያስታግስ በመሆኑ ቁጥጥሩ ሊበረታ ይገባል ተባለ፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድም ካለፈው ሐምሌ 2 ጀምሮ የውጭ አገር ዜጎችን የትኬት አገልግሎት የሚያገኙት በውጭ ምንዛሬ ብቻ ይሆናል ብሏል፡፡


• ሆቴሎች የውጭ ፓስፖርት የያዘን ግለሰብ በብር ማስተናገድ የሚችሉት ይዞት የመጣውን የውጭ ምንዛሬ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ በህጋዊ መንገድ ወደ ብር የመነዘረበትን ተመጣጣኝ ሰነድ ካገኙ ብቻ ይሆናል፡፡


• ኢትዮጵያውያን ወደ ውጭ ለሚያደርጉት በረራ እንደቀድሞው በብር ትኬት መቁረጥ ይችላሉ፡፡


• በኢትዮጵያ ያሉ የተለያዩ ሃገራት አየር መንገዶች ጨምሮ የውጭ ሃገር ዜጎችን (የዲፕሎማቲክ ፈቃድ ያላቸውን ጨምሮ) በውጭ ምንዛሬ ብቻ የትኬት አገልግሎት እንዲሰጡ ይገደዳሉ፡፡



ትዕግስት ዘሪሁን



Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page