top of page

ሐምሌ 12፣2015 - ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ተጨማሪ ክስ ሊመሰረትብኝ ይችላል አሉ

  • sheger1021fm
  • Jul 19, 2023
  • 1 min read

ጉዳዩ ከ3 ዓመታት በፊት የአሜሪካ እንደራሴዎች መምከሪያ የሆነው ካፒቶል ሂል በትራምፕ ደጋፊ ነውጠኞች ከተወረረበት ድርጊት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ፖለቲኮ ፅፏል፡፡


ትራምፕ በዚህ ጉዳይ ክስ እንደሚመሰረትባቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ነግረውኛል በሚል በድረ ገፅ ላይ ፅሁፍ ማስፈራቸው ታውቋል፡፡


ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ብሎ ከሀላፊነት ከተነሱ በኋላ በጣም በርካታ ጥብቅ መንግስታዊ ሚስጥራዊ ሰነዶችን በመኖሪያ ቤታቸው አከማችተዋል በተባለበት ጉዳይ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡


ትራምፕ አስቀድሞ የችሎት ጉዳያቸው ከአሜሪካ ምርጫ በኋላ እንዲሆንላቸው ጥያቄ እያነሱ ነው፡፡


የቀድሞው ፕሬዘዳንት በመጪው አመት ምርጫ ሪፖብሊካዊውን የፖለቲካ ማህበር ወክለው በፕሬዘዳታዊ እጩነት ለመቅረብ ከተነሱ ቆይተዋል፡፡


የኔነህ ከበደ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page