top of page

ሐምሌ 23፣2016 - በባህር ዳር ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ሀይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናግሯል

  • sheger1021fm
  • Jul 30, 2024
  • 1 min read

በባህር ዳር ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ሀይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናግሯል፡፡


የሀይል አቅርቦቱ የተቋረጠው ከትናንት ምሽት 1፡00 ጀምሮ እንደሆነም ተቋሙ ጠቅሷል፡፡


በከፍተኛ መስመር ላይ ባጋጠመ ጉዳት ለሀይል አገልግሎት መቋረጡ ምክንያት ነው ብሏል፡፡


ጉዳት የደረሰው፤ በባህር ዳር ቁ.2 የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በተዘረጋ 15 ኪ.ቮ ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ኬብል ላይ መሆኑንም ተናግሯል፡፡


በዚህም፤ በአየርሀይል፣ በመኮድ፣ በአየር መንገድ፣ በውሃ ጉድጓዶች፣ በቀበሌ 14 እና 16 ባሉ ፋብሪካዎች፣ በቀበሌ 13፣ 14 እና 16 እንዲሁም በአሚኮ፣ በወገልሳ፣ በዘጌ፣ በላታ፣ በጭንባ፣ በከይባብ፣ በመራዊና አካባቢዎቻቸው የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተቋርጧል።


ተቋሙ፤ የተቋረጠውን አቅርቦት ለመመለስ ጥረት እያደረኩ ነውም ብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page