top of page

ሐምሌ 27፣2015 - አትሚስ በሶማሊያ የወታደሮች ቅናሽ ማድረጌን እቀጥላለሁ አለ

  • sheger1021fm
  • Aug 3, 2023
  • 1 min read

በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት /አትሚስ/ በዚያ የወታደሮች ቅናሽ ማድረጌን እቀጥላለሁ አለ፡፡


ለሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ሰራዊት ተልዕኮ ሰራዊት ያዋጡ አገሮች የጦር ሹሞች በቅርቡ በርዕሰ ከተማዋ ሞቃዲሾ በጉዳዩ ላይ እንደተነጋገሩ ዘ ኢስት አፍሪካን ፅፏል፡፡


አዛዦቹ በመጪው መስከረም ወር ተጨማሪ 3 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያስወጡ ተናግረዋል፡፡


አትሚስ ከሰራዊት ቅናሽ በተጨማሪ ደረጃ በደረጃ የጦር ሰፈሮችንም በማስረከብ ላይ ይገኛል፡፡


እስካሁንም 6 የጦር ሰፈሮችን ማስረከቡን ዘገባው አስታውሷል፡፡


አትሚስ ደረጃ በደረጃ ወታደሮቹን እየቀነሰ ቢሆንም በአገሪቱ የአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ስጋትነት ገና እንዳልቀነስ ይነገራል፡፡


የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz


Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page