top of page

ሐምሌ 30፣2016 - ተፈናቃዮች የተጠለሉበት የመጠለያ ጣቢያዎች ዝናብና ነፋሱን መቋቋም ስላልቻሉ ተፈናቃዮቹ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል እያሉ ነው

  • sheger1021fm
  • Aug 6, 2024
  • 1 min read

በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች የተጠለሉበት የመጠለያ ጣቢያዎች ዝናብና ነፋሱን መቋቋም ስላልቻሉ ተፈናቃዮቹ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል እያሉ ነው፡፡


መጠለያም የሚሰጠንም ሆነ ያሉትን የሚጠግንልን አጥተናል ብለዋል፡፡


የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት በበኩሉ ስለችግሩ ለክልሉም ሆነ ለፌደራል መንግስት አሳውቄ መልስ ማግኘት አልቻልኩም ብሏል፡፡


በጃራ መጠለያ ጣቢያ 11,386 ተፈናቃዮች ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን የመጠለያ ጣቢያ ችግር እንደገጠማቸው ተናግሮዋል፡፡


ችግሩ ጃራ የመጠለያ ጣቢያ ብቻ ሳይሆን ወልድያ እና ሀብሩ ወረዳ መርሳ ከተማ እንዲህ ዓይነቱ ችግር እንደገጠማቸው የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ይመር ተናግረዋል፡፡



Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page