top of page

መጋቢት 21፣2016 - ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ለመወያየት ቀጠሮ መያዛቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Mar 30, 2024
  • 1 min read

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሁሉም የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ለመወያየት ቀጠሮ መያዛቸው ተሰማ፡፡


ከሰኞ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ወይይት ይደረጋል፤ በማጠቃለያው ቀንም ለፓርቲ መሪዎቹ ስልጠና ይሰጣል ተብሏል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ አዲስ አበባ ከክልል ያልጠሯቸው የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች አዲስ አበባ መድረሳቸውን ከምንጮቻችን ሰምተናል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለውይይት የጠሯቸው የሀገር አቀፍ እና የክልል የፖለቲካ ፓርቲ የበላይ ሀላፊዎችን ነው ተብሏል፡፡


ለሀገር አቀፍ ፓርቲ ሊቀመንበር ምክትል እና የፅ/ቤት ሀላፊ እንዲሁም ሶስት የስራ አስፈፃሚ አባላትን በድምሩ ስድስት ሰዎችን ለክልል ፓርቲዎች ደግሞ ሊቀ መንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር እና የፅ/ቤት ሀላፊ በድምሩ ሶስት ሰዎች ናቸው የተጠሩት ተብሏል፡፡


ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ግብዣ ኮከስ በሚል የተመሰረተው እና 13 አባላትን የያዘው የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብሰብ ጥሪውን አለመቀበሉንም ምንጮቻችን ነግረውናል፡፡


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page