top of page

መጋቢት 26፣2016 - የሪል ስቴት ዘርፍ የሚመራህግ ባለመኖሩ ቤት ገዢዎች ካርታ ለማግኘት እየተቸገሩ መሆኑንን ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Apr 4, 2024
  • 1 min read

ቢሊዮን ብር የሚገላበጥበት የሪል ስቴት ዘርፍ የሚመራ እና የሚተዳደርበት ህግ ባለመኖሩ በተለይ ቤት ገዢዎች ካርታ ለማግኘት እየተቸገሩ መሆኑንን ተነገረ፡፡


መንግስት በበኩሉ ችግሩን አውቀዋለሁ ለመፍትሄውም እየሰራሁ ነው ብሏል፡፡


እነዚህ ቤት ገንቢዎች ከመንግስት መሬቱን ከተረከቡ በኋላ በራሳቸው ስም በማድረግ ካርታውን በመያዝ ከባንክ ብር እየተበደሩ እንደሚጠቀሙ እና ለባለቤቱ ካርታውን በጊዜ እንደማያስረክቡ ተነግሯል፡፡


ይሁን እንጂ ይህ ሁሉንም ቤት ገንቢዎች አያካትትም ተብሏል፡፡


የዛሬ ሶስትና አራት አመት 60 እና 70 ሺህ ብር የነበረው ካርታን ወደ ራስ ማዞሪያ በዚሁ በሪል እስቴት ገንቢዎች ማንዛዛት ምክንያት፤ አሁን ላይ ቤት ገዢዎች መንግስት ከሰባት መቶ ሺህ ብር በላይ እየጠየቀን ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ማርታ በቀለ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page