top of page

መጋቢት 4 2017 - በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ትጥቅ አስፈትቶ መልሶ ማቋቋም ባለመቻሉ በትግራይ ግዙፍ የታጠቀ ሀይል መኖሩን አቶ ጌታቸው ተናገሩ

በትግራይ ክልል የተፈጠረውን ቀውስ በተመለከተ ከፌዴራል መንግስት ጋር ለመመካከር ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸውን የክልሉ አስተዳደር ፕሬዘዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ፡፡


ክልሉ እየታመሰ እና ጊዜያዊ አስተዳደሩም እየተፈተነ ያለው በፖሊስ አካላት ብቻ ሥርዓት መያዝ በሚችሉ ችግሮች ነው ሲሉም ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡፡


በመሆኑም ክልሉ የፌዴራል መንግስቱ አካል እንደመሆኑ ክልሉ ወደ እርስ በርስ ጦርነት ዳግም እንዳይገባ ሁሉንም አማራጮችና እርምጃዎች ሁሉ መውሰድ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ትጥቅ አስፈትቶ መልሶ ማቋቋም ባለመቻሉ በትግራይ ግዙፍ የታጠቀ ሀይል መኖሩን አቶ ጌታቸው ጠቅሰዋል፡፡


ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር አለመግባባት ውስጥ ከገባው የሕወሃት ቡድን ጋር የጥቅምና ሌላም ትስስር ያለው የታጠቀው የተወሰነ የሰራዊቱን አካል ችግር እየፈጠረ መሆኑንም በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡


የፌዴራል መንግስት አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎች ይውሰድ ስንልም ጦር አዘምቶ ጦርነት ይቀሰቅስ እያልን አይደለም ያሉት አቶ ጌታቸው ወደ ጦርነት እያንዣበበ ያለውን ሁኔታ ለማስቀረት ሁሉንም ዓይነት እርምጃ እንዲወስድ እንፈልጋለን ብለዋል፡፡


በድምፅ ያድምጡ…






ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page