top of page

ሚያዝያ 11 2017 - በዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የኢ-ኮሜርስ አገልግሎት መጀመሩን ተናገሩ

  • sheger1021fm
  • 6 minutes ago
  • 1 min read

በዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የኢ-ኮሜርስ አገልግሎት መጀመሩን ተናገሩ።


በፋይናንስ ኢንዱስትሪው አዳዲስ የዲጂታል ግኝቶችን እያስተዋወቀ እንደሆነ የተናገረው ዳሸን ባንክ፣ በዳሸን ሱፐር አፕ የኢ-ኮሜርስ አገልግሎት መጀመሩን ተናግሯል።


ደንበኞች በዳሸን ሱፐር አፕ ለበዓል የሚያስፈልጋቸውን የበሬ ቅርጫ፣ የበግ እና የዶሮ ስጋ አንቁላልን ጨምሮ አልባሳት፣ ለስጦታ የሚሆኑ ሰዓትና ቀለበቶች፣ ዘመናዊ የቆዳ ቦርሳዎች ዘመናዊ ጫማዎች፣ የባልትና ወጤቶች እና ሌሎች በርካታ ምርቶችን በቀላሉ መገበያየት ይችላሉ ሲል ለሸገር በላከው መግለጫ አስረድቷል፡፡



ዳሸን ባንክ ይፋ ያደረገው የኢ-ኮሜርስ አገልግሎት ደንበኞች በዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የፈለጉትን እቃ በቀላሉ ሲያዙ፣ ከየትኛውም የአዲስ አበባ አካባቢ ባሉበት ሆነው የታዘዘው ዕቃ በፍጥነት የሚደርሳቸው ይሆናል ተብሏል፡፡


ዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ የኢ-ኮሜርስ አገልግሎት ሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶችን ይዞ እየመጣ እንደሚገኝ ባንኩ አስረድቷል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…






Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page