top of page

ሚያዝያ 14 2017 - በጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይት ላይ፤ ወጥ የሆነ ዋጋ እንዲኖረው ሊደረግ መሆኑ ተሰማ

  • sheger1021fm
  • 6 minutes ago
  • 1 min read

በጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይት ላይ፤ ወጥ የሆነ ዋጋ እንዲኖረው ሊደረግ መሆኑ ተሰማ።


የጥሬ ቆዳና ሌጦ ግብይትን በተመለከተ የዋጋ ወጥነት ባለመኖሩ በተለይ በበዓላት ወቅት በየመንገዱ እንዲወድቅ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል።


ይህንን እና መሰል ችግሮችን ይቀርፋል፣ የተባለለት ይህ አሰራር በቅርቡም ወደ ስራ እንደሚገባም የነገረን የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንደስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ነው።


በአምራች ኢንደስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ቆዳና #የቆዳ_ውጤቶች ኢንደስትሪ ግብአት ዴስክ ሀላፊ አቶ ታረቀኝ ዲዳ ይሄ አሰራር ተግባራዊ ሲደረግ ነጋዴዎች አላግባብ የሚጥሉትን ዋጋ እንዲቆጣጠር ያስችላል ብለዋል።



ከዚህ ቀደም በቆዳው ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች ከዘርፉ የወጡ እንደነበሩ ያስታወሱት አቶ ታረቀኝ በዘርፉ የወጡበት ምክንያት የገበያ ትስስር፣ የኬሚካል አቅርቦት እና የጨው አቅርቦት አለመኖር እንዲሁም መሰል ችግሮች ስለነበሩ ነው ሲሉ አስረድተዋል።


አሁን ላይ ግን በተወሰነ መልኩ የተፈቱ ችግሮች ቢኖሩም የኬሚካል አቅርቦት ግን አሁንም ዘርፉን እየፈተነው መሆኑን ነግረውናል።


ከዚህ ቀደም በየመንገዱ ይጣል የነበረው ቆዳ አሁን እምብዛም አይታይም ያሉን አቶ ታረቀኝ በማህበረሰቡ በኩል ግን አሁንም ቆዳ ዋጋ የሌለው አይነት አመለካከት እንዳለም ተናግረዋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page