top of page

ታህሳስ 13፣2016 - ‘’በግዴታ ወደ ነበራችሁበት ካልተመለሳችሁ የዕለት እርዳታ አታገኙም’’

  • sheger1021fm
  • Dec 23, 2023
  • 1 min read

በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚያጋጥሙ የፀጥታ ችግሮች፣ ግጭቶች እና ጥቃቶች ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያው ተጠልለው ዓመታትን ያስቆጠሩ ሚሊዮኖች ናቸው፡፡


ኢትዮጵያ ተቀብላ ባፀደቀቺው የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን አያያዝና መብት የሚመለከተው የካምፓላው ስምምነት ተፈናቃዮች በ6ወር ውስጥ ተመልሰው መቋቋም እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡


በተጨማሪም መልሰው ሲቋቋሙ የተፈናቃዮቹን ሀሳብ ሊከበር እንደሚገባም እንዲሁ፡፡


ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተፈናቀሉባቸው አካባቢዎች የሰላም ሁኔታ ሳይረጋገጥ በግዴታ ወደ ነበራችሁበት ካልተመለሳችሁ የዕለት እርዳታ አታገኙም የሚል ግፊት በርትቶብናል የሚሉ ተፈናቃዮች እየበዙ ነው፡፡


በጉዳዩ ላይ በደብረ ብርሃን የተጠለሉ የ40,000 ስደተኞች ተወካዮቻቸውን ጠይቀናል፡፡


ማርታ በቀለ





የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page