top of page

ታህሳስ 7፣ 2015- የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ በሀላፊነት ላይ የሚገኙትን ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሣን በፍርድ ቤት መክሰሳቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Dec 16, 2022
  • 1 min read

የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ በሀላፊነት ላይ የሚገኙትን ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሣን በፍርድ ቤት መክሰሳቸው ተሰማ፡፡


ዙማ በጆሃስበርግ ፍርድ ቤት በግል በራማፎሣ ላይ ክስ መመስረታቸውን በስማቸው የተቋቋመ ድርጅት እወቁልኝ ማለቱን ዘ ሳውዝ አፍሪካን ፅፏል፡፡


ጉዳዩ ከፋላ ፋላው አጋጣሚ ጋር የተገናኘ ነው ተብሏል፡፡


ከፕሬዝዳንቱ የፋላ ፋላ እርስት በውጭ ምንዛሪ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ መዘረፉን ሸፋፍነዋል በሚል ሪፖርት ከወጣ በኋላ ራማፎሣ ጫና በርትቶባቸው ሰንብቷል፡፡


ፕሬዝዳንት ራማፎሣ የዙማን ክስ አይረቤ እና መሰረተ ቢስ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


በደቡብ አፍሪካ የገዢው የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ANC የፖለቲካ ማህበር አገራዊ ሸንጎ ዛሬ መሪውን ይመርጣል ተብሏል፡፡


በጫና ውስጥ የከረሙት ሲሪል ራማፎሳ አንዱ ተፎካካሪ መሆናቸው ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page