top of page

ነሐሴ 15፣2016 - በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ኃይል ሊቋረጥ እንደሚችል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ተናገረ

በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ኃይል ሊቋረጥ እንደሚችል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ተናገረ፡፡


የኤሌክትሪክ ሀይል የሚቋረጠው ወደ ተከዜ የኃይል ማመንጫ ግድብ የሚገባውን ውሃ በማስተንፈስ ሂደት የጣቢያው ዩኒቶች ሥራ በማቆማቸው ነው ብሏል፡፡


ከግድቡ ውሃ ሲለቀቅ የሚፈጠረው የእንፋሎት ጭጋግ በትራንስፎርመሮችና የኃይል ማመንጫ ቤቱ ላይ ጉዳት እንዳያስከትል ሁለቱ ዪኒቶች እንዲቆሙ ተደርጓል ተብሏል።


በዚህም የቮልቴጅ መዋዠቅ አጋጥሟል ብሏል ተቋሙ፡፡


በዚህ አጋጣሚ ከግድቡ በላይኛውና በታችኛው ተፋሰስ በሚገኙት፤


በጣንቋ፣ አበርገለ፣ በቆላ ተንቤን፣ በላዕላይ እና ታህታይ ማይጨው፣ በመረብለኸ፣ በአስገደ ጽንበለ፣ በላዕላይና ታህታይ አዲያቦ፣ በመደባይ ዛና፣ በታህታይ ቆራሮ፣ በአጠቃላይ የተከዜ ወንዝ ተዋሳኝ በሆኑ ወረዳዎች ነዋሪዎችና የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ተናግሯል ።


የክረምቱ ዝናብ እና ወደ ግድቡ የሚገባው የውሃ መጠን እስከሚቀንስ ድረስ ችግሩ ለቀናት እንደሚቀጥልም ተጠቁሟል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page