top of page

እስራኤል በዌስት ባንክ ጄኒን ከተማ ድብደባ እየፈፀመች ነው

  • sheger1021fm
  • Jul 3, 2023
  • 1 min read

ሰኔ 26፣2015


እስራኤል በዌስት ባንክ ጄኒን ከተማ ድብደባ እየፈፀመች ነው፡:


ዛሬ ማለዳ እስራኤል በጀኒን ከተማ በሚገኘው የፍልስጤማውያን የስደተኞች ሰፈር ላይ በፈፀመችው የአየር ጥቃት በጥቂቱ 3 ሰዎች እንደተገደሉ አናዶሉ ፅፏል፡፡


13 ሰዎች ደግሞ የተለያየ ደረጃ አካላዊ ጉዳት ገጥሟቸዋል ተብሏል፡፡


እስራኤል የጄኒኑ የስደተኞች ሰፈር የአሸባሪዎች ምሽግ ነው ትላለች፡፡


ከአየር ድብደባውም በኋላ የእስራኤል እግረኛ ወታደሮች ወደ ጀኒን የስደተኞች መጠለያ ሰፈሩ እየገፉ ነው ተብሏል፡፡


ፍልስጤማውያን ታጣቂ ቡድኖች ፣ ሐማስ ፣ ኢስላማዊ ጂሃድ እና የፈታህ ንቅናቄ ወታደራዊ ክንፍ ተባብረን እስራኤልን እንፋለማታለን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


በእስራኤል የዌስት ባንክ የሰፈራ ማስፋፊያ የተነሳ ውጥረት እና ግጭት እየተባባሰ መምጣቱ ይነገራል፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page