መጋቢት 3፣2016 - ከህዝብ አቤቱታ እና ቅሬታ የሚቀበልበትን አጭር የስልክ መስመር በአዲስ በመቀየር ስራ መጀመሩን እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ
- sheger1021fm
- Mar 12, 2024
- 1 min read
ከህዝብ አቤቱታ እና ቅሬታ የሚቀበልበትን አጭር የስልክ መስመር በአዲስ በመቀየር ስራ መጀመሩንየኢትዮጵያ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡
አዲሱ ጥቆማ የሚቀበልበት አጭር የስልክ መስመር ቁጥርም 9503 ነው ተብሏል፡፡
ከዚህ በፊት ከህዝብ አቤቱታ እና ቅሬታ ይቀበልበት የነበረው አጭር የስልክ መስመር ስራ በማቆሙ ይደርሰው ከነበረው አቤቱታ በአንድ አራተኛ ቀንሶ እንደነበረም ተቋሙ አስታውሷል፡፡
ምንታምር ፀጋው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Website: https://www.shegerfm.com/
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Commenti