top of page

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሰሞኑ የዋግነር አመፅ የማነሳሳት ሙከራ ጀርባ የምዕራባዊያን እጅ ስለመኖሩ እየመረመርን ነው አሉ

  • sheger1021fm
  • Jun 29, 2023
  • 1 min read

ሰኔ 20፣2015


የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከሰሞኑ የዋግነር አመፅ የማነሳሳት ሙከራ ጀርባ የምዕራባዊያን እጅ ስለመኖሩ እየመረመርን ነው አሉ፡፡


ላቭሮቭ በዋግነር የተነሳው አመፅ እንደሚሳካ በአሜሪካ የደህንነት መስሪያ ቤቶች አስቀድሞ ተስፋ ተደርጎ እንደነበር ማንሳታቸውን አል አረቢያ ፅፏል፡፡


እንደውም የአሜሪካ የደህንነት ሹሞች ከዋግነሮች አመፅ መቀስቀስ አስቀድሞ ምልክቶችን አይተናል ማለታቸውን ላቭሮቭ ተናግረዋል፡፡


አመጹ በ24 ሰዓታት ጊዜ መክኗል፡፡


በጉዳዩ የምዕራባዊያን እጅ እንዳለበት ለማወቅ በሩሲያ የደህንነት መስሪያ ቤት እየተመረመረ መሆኑን ላቭሮቭ ተናግረዋል፡፡


የስልጡን ቅጥረኛ ወታደሮች አቅራቢው የዋግነር ኩባንያ የበላይ እና የአመፁ መሪ ውጥናቸውን ትተው ወደ ቤላሩስ ማምራታቸው ታውቋል፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page