top of page

የካቲት 13 2017 - በአለም ከአንድ  መቶ በላይ ሀገሮች የሆቴል አገልግሎት የሚሰጠው ሒልተን ሆቴል በአዳማ እና በድሬዳዋ ሆቴሎች ሊከፍት መሆኑ ተሰማ

በአለም ከአንድ  መቶ በላይ ሀገሮች የሆቴል አገልግሎት የሚሰጠው ሒልተን ሆቴል በአዳማ እና በድሬደዋ ሆቴሎች ሊከፍት መሆኑ ተሰማ፡፡


ሆቴሎቹ  ከ3 ዓመት በውሀላ በአዳማ እና በድሬዳዋ ይከፈታሉ መባሉን  ኦል አፍሪካ ፅፏል።


ኩባንያው በኢትዮዽያ የተለያዩ ስምንት ንብረቶችን ለማስተዳደርም በእቅዱ አስፍራል።


ደብል ትሪ ባይ ሂልተን የተሰኝው ብራንድ ከ24ቱ በሂልተን ከሚተዳደሩ ሆቴሎች አንደኛው ነው።


በአዳማ የሚገነባው  ይህ ሆቴል ከአዲስ አበባ ጋር በሚያገናኘው ዋና መንገድ ላይ የሚሰራ ነው ተብሏል፡፡


በአዳማ የሚሰራው ደብል ትሪ ባይ ሂልተን 188 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች ይኖሩታል ሲል የወሬ ምንጩ ዘግቧል፡፡


የድሬዳዋው ድግሞ 150 የእንግዳ ማረፊያ ይኖሩታል ተብሏል፡፡



ሁለቱም የሂልተን ሆቴሎችና ሰፊ ማረፊያዎች ለተጓዦች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ከፍ ያለ የምግብ እና የመጠጥ አማራጮችን ይሆናሉ።


ሂልተን በተለያዩ ሀገሮች ቅንጡና አለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቁ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሆቴሎች እንዳሉት ይታወቃል።


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page