top of page

የካቲት 14 2017 -የኢሜግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ኢ-ፓስፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡

የኢሜግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ኢ-ፓስፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡


የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርቱ የግለሰቦችን መረጃና የጣት አሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክ ችፕስ የያዘ መሆኑ ተሰምቷል፡፡


አዲሱ ፓርፖርት በአገር ውስጥ የታተመና ከፍተኛ የደህንነት ደረጃ እንዳለው ሰምናል፡፡

አዲሱ የኢትዮጵያ ኢ-ፓስፖርት የኢሜግሬሽን ሒደት የሚያቀላጥፍ እንደሆነ ሰምናል፡፡


በሃገር ውስጥ የሚታተመው ፓስፖርቱ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን መመዘኛዎች ያሟላና አለም አቀፍ ተቀባይነትን ያረጋገጠ መሆኑ ተነግሯል፡፡


ከዚህ በተጨማሪም የኢሜግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለውጭ አገር ዜጎች የሚሰጠውን ቪዛ በአዲስ ህትመት እና ይዘት በአገር ውስጥ ታትሞ አገልግሎት ላይ እንደሚውል ሰምተናል፡፡


የኢሜግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በስራ ላይ የነበረው የአስቸኳይ የጉዞ ሰነድ በወረቀት ይታተም የነበረ በመሆኑ የሌላ አገር ዜጎች ስደተኛ ነን በማለት ከአገር ይወጡበት እንደነበር መናገሩ ይታወሳል፡፡


ይህ አሰራር አሁን ላይ ወደ ዲጂታል መቀየሩን ተከትሎ ተመሳሳይ ማጭበርበር እንደማይኖር ከኢሜግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሰምተናል፡፡


ኢ-ፓስፖርቱ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በቶፖን ሴክዩሪቲ ኢትዮጵያ አክሲዮን ማህበር አማካኝነት አገር ውስጥ መመረቱን ሰምተናል፡፡


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page