top of page

የካቲት 14 2017 - ''የጥናት እና ምርምር ስራዎች ቢኖሩም ጊዜ የላቸውም በሚል እንድንሳተፍ እድል አይሰጠንም''

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሰሩ ሴት ተመራማሪዎች ቁጥር ካለፈው ጊዜ የጨመረ ቢሆንም ከአጠቃላይ ቁጥሩ አንፃር ግን አሁንም በቂ አይደለም ተባለ፡፡


ከአራት ዓመት በፊት በተጠና ጥናት መሰረትም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ሴቶች 16.9 በመቶ መሆኑን ያሳያል፡፡


በሌላ በኩል ደግሞ አዳዲስ ሴት ተመራማሪዎችን ወደ መስመሩ ከማምጣት ባለፈም ያሉትም ቢሆን የሚገጥሟቸው ችግሮች ቀላል አለመሆናቸውን ጥናት አሳይቷል፡፡


ከጊዜ ወደ ጊዜ በዘርፉ የሴቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ጥናት ያሳያል የተባለ ሲሆን አሁን ያለው ቁጥር ግን በቂ አይደለም፤ ያሉትም ቢሆን ብዙ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ቆይቷል ተብሏል፡፡


ተቋማት ብቻ ሳይሆኑ የስራ ባልሰደረቦችም የተሳሳተ አመለካከት አለ፤ ጥናት እና ምርምር ስራዎች ቢኖሩም ጊዜ የላቸውም በሚል እንድንሳተፍ እድል አይሰጠንም ይላሉ፡፡


ሴቶቹ ባሉበት ዘርፍ ወደፊት እንዳይመጡ እንቅፋት ከሆነባቸው ችግሮች መካከል ሌላኛው ደግሞ በተቋሙ ያለው መዋቅር ውስብስብ መሆኑ ነው መባሉን ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ ….



ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page