top of page

የካቲት 15፣2015 - የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን እንድረዳቸው እርዱኝ አለ

  • sheger1021fm
  • Feb 23, 2023
  • 1 min read


የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን እንድረዳቸው እርዱኝ አለ፡፡


ኮሚሽኑ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን ለመርዳት የ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር የተማፅኖ ጥያቄ ማቅረቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡


በአቅራቢያው አገሮች 2 ነጥበ 2 ሚሊዮን ስደተኞች እንደሚኖሩ ዘገባው አስታውሷል፡፡


ኮሚሽኑ ስደተኞቹን ለማኖር የእርዳታ ገንዘቡ በእጅጉ አስፈላጊ ነው ማለቱ ተሰምቷል፡፡


ከደቡብ ሱዳን ስደተኞች 80 በመቶዎቹ በቀጠናው ይገኛሉ ተብሏል፡፡


አገሪቱ ለበርካታ አመታት ግጭት ውስጥ ቆይታለች፡፡


አሁንም ድረስ ወደ ሙሉ መረጋጋት መመለስ እንዳልቻለች ዘገባው አስታውሷል፡፡



የኔነህ ከበደ





ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page