የካቲት 15፣2015 - የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን እንድረዳቸው እርዱኝ አለ
- sheger1021fm
- Feb 23, 2023
- 1 min read

የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን እንድረዳቸው እርዱኝ አለ፡፡
ኮሚሽኑ የደቡብ ሱዳን ስደተኞችን ለመርዳት የ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር የተማፅኖ ጥያቄ ማቅረቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡
በአቅራቢያው አገሮች 2 ነጥበ 2 ሚሊዮን ስደተኞች እንደሚኖሩ ዘገባው አስታውሷል፡፡
ኮሚሽኑ ስደተኞቹን ለማኖር የእርዳታ ገንዘቡ በእጅጉ አስፈላጊ ነው ማለቱ ተሰምቷል፡፡
ከደቡብ ሱዳን ስደተኞች 80 በመቶዎቹ በቀጠናው ይገኛሉ ተብሏል፡፡
አገሪቱ ለበርካታ አመታት ግጭት ውስጥ ቆይታለች፡፡
አሁንም ድረስ ወደ ሙሉ መረጋጋት መመለስ እንዳልቻለች ዘገባው አስታውሷል፡፡
የኔነህ ከበደ
ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
https://bit.ly/33KMCqz
Comments