top of page

የካቲት 20፣2016 - የሰላም ሚኒስቴር በ45 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 9 ጀምሮ በሶስት ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጉን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Feb 28, 2024
  • 1 min read

ርዕሰ ጉዳዮቹ በሀገራዊ ጥቅም፣ ሀገራዊ እሴት እና የጋራ ማንነት ናቸው ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ያህል በሀገራዊ ጥቅም ያምናል፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ብሔሮች የራሳቸው እሴት እንዳላቸው ሁሉ በሀገራዊ እሴት ያምናሉ ወይ፣ ካላቸው የተለያየ ማንነት ባለፈ አንድ በሚያደርግ የኢትዮጵያ ማንነት ላይ ያላቸው አመለካከት ምን ይመስላል? በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ሲሉ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የሰላም ሚኒስትር ድኤታው ከይረዲን ተዘራ አስረድተዋል፡፡


በውይይቱ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን እና ወጣቶች በ45ቱም የትምህርት ተቋማት ተሳትፈዋል ብለዋል፡፡


ተደርጓል በተባለው የውይይት መድረክ ከ20 ሺህ በላይ መምህራን እንደተሳተፉና የትምህርት ተቋማቱ ባላቸው የማህበረሰብ ሬዲዮ ለ40 ሚሊየን ሰዎች ተደራሽ ማድረግ ችለዋል ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል፡፡


በውይይቱና በምክክሩ ላይ የተገኙት ውጤቶች አርብ በአድዋ ሙዚየም ይፋ ይደረጋሉ ተብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Kommentare


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page