top of page

የካቲት 28፣2016 - የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጋዜጠኞች የሚደርስባቸው ጫና እያሳሰበኝ ነው አለ

  • sheger1021fm
  • Mar 7, 2024
  • 1 min read

 የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጋዜጠኞች ከስራቸው ጋር በተገናኘ የሚደርስባቸው ጫና እያሳሰበኝ ነው አለ።

 

ምክር ቤቱ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን በኢሊሌ ሆቴል እያካሄደ ይገኛል።

 

የምክር ቤቱ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ  ስብሳቢ አቶ አማረ አረጋዊ የ2014 እና የ2015 የስራ ክንውንን የተመለከተ ሪፖርት ለጉባኤው አቅርበዋል።

 

በዚህም ጋዜጠኞች በተለያየ ጊዜ ከስራቸው ጋር በተገኘ መታሰራቸውን ፣ የአንዳንዶቹም የስራ ዕቃዎች መዘረፋቸውን ተናግረዋል።

 

ሁኔታው ምክር ቤቱን እንደሚያሳስበው የተናገሩት አቶ አማረ በጉዳዩ ላይ ተደጋጋሚ መግለጫዎች ምክር ቤቱ ማውጣቱን አስታውሰዋል።



 ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን እና ከፀጥታ አካላት የስራ ሃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደንበታልም ብለዋል።

 

በዚህ ውይይትም በጋዜጠኞች ላይ ከስራቸው ጋር በተገናኘ የሚደርስባቸው ጫና እንደሚያሳስበን እና እንደሚያሰጋን አሳውቀናል ሲሉ ተናግረዋል።

 

በጉባኤው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው የምክር ቤቱ መጠናከር የኢትዮጵያን የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ያሳድገዋል ብሎ መንግስት እንደሚያምን ተናግረዋል።

 

 

ንጋቱ ረጋሣ

 


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page