top of page

የካቲት 3 2017 - ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደብላቸው በጀት የሚያስመዘግቡት ውጤት ታይቶ እንደሚሆን ት/ት ሚ/ር መናገሩ ይታወቃል

ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደብላቸው የበጀት ምጣኔ የሚያስመዘግቡት ውጤት ታይቶ ብቻ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር መናገሩ ይታወቃል፡፡


ለዚህም ከ47ቱም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚደንቶች ጋር ተነጋግሬ ከስምምነትም ደርሰናል ብሏል፡፡


ይህ አሰራር ዩኒቨርሲቲዎች ተጠያቂነት እንዲኖርባቸው፣ አሰራራቸውም እንዲፈተሽ ያደርጋልም ተብሎለታል፡፡


ለመሆኑ አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ #ዝቅተኛ ወይም #ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ የሚባለው መቼ ነው? ውጤቱስ በመን አይነት መለኪያ ነው የሚመዘነው?


በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔን አነጋግረናል፡፡


ሚኒስቴር ዴኤታው ዩኒቨርሲቲዎች ውጤታማነታቸው ተመዘኖ ተጠያቂ ጭምር የሚደረጉባቸው መስፈርቶች አሉን ብለውናል፡፡


በአዲሱ አሰራር እንደከዚህ ቀደሙ ተድበስብሶ የሚታለፉ ጉዳዮች አይኖርም ያሉ ሲሆን ለሚፈስባቸው ሀብትም ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያመጡም ይጠበቃል በማለትም ያስረዳሉ፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..




ማንያዘዋል ጌታሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Kommentare


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page