top of page

የካቲት 8፣2016 - አቶ ዱላ መኮንን የዳሸን ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበር ሆነው በድጋሚ ተመረጡ

ተመራጩ ባለፉት ሶስት ዓመታት የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ በሊቀ-መንበርነት መምራታቸው ተሰምቷል።


በድጋሚ የተመረጡትም የባንኩ ባለአክሲዮኖች ባካሄዱት 30ኛው መደበኛ ጉባኤ የተመረጠውና የምርጫውም ውጤት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያፀደቀለት አዲሱ የዳሸን ባንክ ቦርድ ባደረገው የመጀመሪያ ጉባኤ ላይ መሆኑን ሰምተናል።


መጪዎቹን ሶስት ዓመታት ዳሸን ባንክን በዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ-መንበርነት እንዲያገለግሉ በድጋሚ የተመረጡት አቶ ዱላ መኮንን በአሁኑ ወቅት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የማዕድን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ ተብሏል፡፡



አዲስ የተመረጡት የቦርድ አባላት እና ባንኩን ላለፉት ሶስት ዓመታት ያገለገሉት የቦርድ አባላት የስራ ርክክብ ያደረጉ ሲሆን ንዑስ ኮሚቴዎችንም አዋቅረዋል ሲል ባንኩ ለሸገር በላከው መግለጫ ጠቅሷል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


bottom of page