top of page

የካቲት 9፣2016 -ከሰሞኑ ባለስልጣናት ከህዝብ ጋር ያደረጓቸው ውይይቶች ጉዳይ

  • sheger1021fm
  • Feb 17, 2024
  • 1 min read

የትጥቅ ግጭቶች ያሉባቸውን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከህዝብ ጋር ሲወያዩ መሰንበታቸው በመገናኛ ብዙሃን እየተነገረ ነው፡፡


መንግስት ውይይቶቹ የህዝብ መሰረታዊ ጥያቄን የተረዳሁበት እና ከመግባባት የተደረሰባቸው መድረኮችም ናቸው ሲል ይገልፃቸዋል፡፡


ከህዝብ ጋር መወያየት ችግሮችን ለመፍታት ዓይነተኛ መፍትሄ ቢሆንም በውይይት ላይ የሚመለከታቸው ሁሉ ተሳትፈዋል ወይ? የሚለው ግን ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ይላሉ፡፡


ሸገር ያነጋገራቸው የፖለቲካል ሳይንስ መምህር መፍትሄ ለማበጀትም የግድ አሳታፊ እና ሁሉም የተወከለበት ውይይት ቢደረግ ይሻላል ሲሉም ይመክራሉ፡፡


ንጋቱ ረጋሣ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page