የጥቅምት 7፣2017 - እያደገ ነው ለሚባለው የሀገሪቱ ንግድ መፍትሄ ምን ይሆን?
- sheger1021fm
- Oct 17, 2024
- 1 min read
የኢትዮጵያ ወጪ እና ገቢ ንግድ ከ90 በመቶ በላይ በጂቡቲ ወደብ ላይ ጥገኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡
ሀገሪቱ ለወደብ ኪራይ በዓመቱ የምታወጣው ወጪም አንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ተሸጋግሯል ተብሏል፡፡
ይህ ገንዘብ በሰሞነኛው የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ተመን ወደ 115 ቢሊዮን ዳር ይጠጋል፡፡
ይህ የኢትጵያ ገንዘብ በተያዘው በጀት ዓመት በሕዝብ ብዛት ትልልቅ ናቸው ለሚባሉት ማለትም ለኦሮሚያ እና ለአማራ ክልሎች ከተመደበው አመታዊ የፌዴራል መንግስት በጀት ጋር ተስተካካይ ነው፡፡
ይህ ብቻ ሳይሆን አገሪቱ ወደብ አልባ ሆኖ መቆየቱ ምንም ሳንቲም ሳታገኝባቸው በኮትሮባንድ የሚወጡ እና የሚገቡ ምርቶችም ጨምረዋል ተብሏል፡፡
ታዲያ እያደገ ነው ለሚባለው የሀገሪቱ ንግድ መፍትሄ ምን ይሆን?
በቢሊዮን የሚቆጠር የሀገር ሀብት ይዘው የሚንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ መርከቦችስ ድህንነት ጉዳይ አሁን እየጨመረ ከመጣው የባህር ወንበዴ መጠበቅያው መንገድ የቱ ነው?
በአዲስ አበባ የኒቨርሲቲ የሎጂስቲከስ መምህር የሆኑትን ማቲዮስ ኢንሰርሙ(ዶ/ር)ን ጠይቀናል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
Comentarios