‘’የፀጥታ አካላትም የመብት ጥሰት ላይ ተሳታፊ ናቸው’’
- sheger1021fm
- Dec 9, 2023
- 1 min read
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት እየከፋ መምጣቱንና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በዘርፉ ላይ በተሰማሩ ተቋማት እየተነገረ ነው፡፡
የሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩና ሰላማዊና ንጹሃን ዜጎች ከጥቃት እንዲጠበቁ የሚሞግቱ ተቋማት ሰራተኞች ላይ ሳይቀር የተለያየ ጥቃት እየደረሰባቸው መሆኑ የችግሩን ግዝፈት ያሳያል ተብሏል፡፡
የዜጎችን መብት ማስከበር የሚጠበቅባቸው የመንግስት ባለስልጣት እና የፀጥታ አካላት በዜጎች ላይ በሚደርስ የመብት ጥሰት ላይ ተካፋይ መሆናቸውን ሪፖርቶች ቢያሳዩም ተጠያቂ አለመደረጋቸው ደግሞ ችግሩን ያበረታዋል ይላሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፡፡
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Comments