top of page

ግንቦት  2፣2016 - አቢሲንያ ባንክ የሴቶች ቀን  አስመልክቶ ባዘጋጀው የተለያየ ውድድር አሸናፊዎቹን ሸለመ

  • sheger1021fm
  • May 10, 2024
  • 1 min read

አቢሲንያ ባንክ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን  ማርች 8 አስመልክቶ ባዘጋጀው የተለያየ ውድድር አሸናፊዎቹን ሸለመ፡፡

 

ባንኩ ለ3ተኛ ጊዜ ባዘጋጀው እና ‘’እችላለሁ’’ ሲል በሰየመው መርሐ ግብር በድምፅና በቲክ ቶክ አጭር ቪዲዮ ሰርተው ከ1-3 ደረጃን ላገኙ ሴቶች የገንዘብ ሽልማት መሰጠቱን ተናግሯል፡፡

 

እንዲሁም በሥራ ፈጠራ ተወዳድረው አሸናፊ ለሆኑ እንስቶች ለሥራ ማስፋፊያ የሚሆን አነስተኛ ወለድ ያለዋስትና ብድር ማመቻቸቱንም ባንኩ ለሸገር በላከው መግለጫ አስረድቷል፡፡

ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 30/2024  ባሉት ቀናት ውስጥ በድምፅ፣ በቲክ ቶክ አጭር ቪዲዮ እና በሥራ ፈጠራ ለመወዳደር ፍላጎቱ ያላቸው ሴቶች የመወዳደሪያ ሥራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ የተደረገ ሲሆን፣ በዘርፉ አንቱ በተባሉ ባለሞያዎች እና ከሕዝብ በተሰበሰበ ድምጽ አሸናፊዎች እንዲለዩ ተደርጓል ተብሏል፡፡

 

በዚሁ የሽልማት መርሐ-ግብር ላይ የሰባት ዓመት ዕድሜ ያላቸውን ሦስት መንታ ሕፃናትን ለውጭ ሀገር የሕክምና ወጪያቸው የሚያግዛቸውን የ ሦስት መቶ ሺህ ብር ባንኩ ድጋፍ ማድረጉንም ጠቅሷል፡፡

ባንኩ ለ3ተኛ ጊዜ የተካሄደውን የ2024 ዘመቻን አካቶ በሥራ ፈጠራ፣ በግጥም፣ በድምፅ እንዲሁም በቲክ ቶክ አጭር ቪዲዮ ተሰጥዖ ያላቸውን ሴቶች አወዳድሮ መሸለሙ፣ ያላቸውን ተሰጥዖ እንዲያጎለብቱና ለሕዝብ በተሻለ እንዲደርሱ መደላድልን ፈጥሯል ተብሏል፡፡

 

አቢሲንያ ባንክ ከተቋቋመ የ28 ዓመታት ዕድሜን ያስቆጠረ ሲሆን በኃብትና ካፒታል እድገት፣ በአጠቃላይ ገቢ፣ በተቀማጭ ገንዘብ፣ በብድር፣ በትርፍ፣ በቅርንጫፍ ብዛት እና በአስቀማጭ ደንበኞች ቁጥር የላቀ አፈጻጸም እያስመዘገበ አንደሆነ ተናግሯል፡፡

 

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page