top of page

ግንቦት 22፣2016 - ኢሰመኮ በግል ስራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች መብት ዙሪያ ከሰጠኋቸው ምክረ ሃሳቦች አብዛኞቹ አልተተገበሩም አለ

  • sheger1021fm
  • May 30, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በግል ስራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች መብት ዙሪያ ከሰጠኋቸው ምክረ ሃሳቦች አብዛኞቹ አልተተገበሩም አለ።


የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግል ስራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞችን መብቶች የተመለከተ ሪፖርት፤ እና ምክር ሃሳብ መስከረም ወር ላይ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።


ኮሚሽኑ በሪፖርቱ በግል ስራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች አማካይነት ተቀጥረው በሚሰሩ ሠራተኞች መብቶች ላይ ችግሮች እንደሚታዩ ጠቁሞ ነበር።


በተለይም ምቹ የስራ ሁኔታና ማህበራዊ ዋስትና የማግኘት፣ የመደራጀት እና ቅሬታ የማሰማት እንዲሁም በፍትህ መብቶች አተገባበር ላይ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ ጠቅሷል።


በእነዚህ ችግሮች ላይ የማስተካከያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ምክረ ሃሳቦች አቅርቦ እንደነበርም፤ በኮሚሽኑ የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ስራ ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር ብራይትማን ገብረሚካኤል አስታውሰዋል።


ይሁን እንጂ አብዛኞቹ ምክረ ሃሳቦች እየተተገበሩ አይደለም ነው ያሉት።

ree

ሰራተኛው ከደመወዙ ቢያንስ 20 በመቶውን ማግኘት አለበት በሚለው ደንብ አፈጻጸም ላይ፤ በፍርድ ቤቶች አካባቢ ጭምር ልዩነቶች መታየታቸውን ዶክተር ብራይትማን ነግረውናል።


ኮሚሽኑ ከሰጣቸው ምክር ሃሳቦች መካከል የተፈጸሙ እና በበጎ የሚታዩ አሉ ሲሉም ዳይሬክተሩ ነግረውናል።


የኤጀንሲ ሰራተኞች ጉዳይ የሶሰትዮሽ ግንኙነት እንደሆነ የሚናገሩት ዶክተር ብራይትማን፤ ይህንኑ ልዩ ባህሪያቸውን ከግምት ያስገባ የህግ ማዕቀፍ ሊዘጋጅ ይገባል የሚል አቋም ኮሚሽኑ እንዳለውም ነግረውናል።


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw


Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio


Website: https://www.shegerfm.com/


Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page