ግንቦት 26፣2016 - የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እስረኞችን በሃገራዊ ምክክሩ ለማሳተፍ እየሰራሁ ነው አለ
- sheger1021fm
- Jun 3, 2024
- 1 min read
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በህግ ጥላ ስር የሚገኙ እስረኞችን በሃገራዊ ምክክሩ ለማሳተፍ እየሰራሁ ነው አለ፡፡
በምክክሩ ሂደት አጀንዳዎችን በማሰባሰብ ላይ የሚገኘው ኮሚሽኑ በተቻለ መጠን ሁሉም ይሳተፋል፤ አንድም የሚቀር የማህበረሰቡ ክፍል የለም ብሏል፡፡
ሁሉም ተሳታፊ፤ ለምክክሩ ይበጃል ሊመከርበትም ይገባል የሚለውን አጀንዳ እያቀረበም ይገኛል፡፡
በተለያዩ ምክንቶች ተጠርጥረው የታሰሩ፤ በተለይም በፖለቲካ እንቅስቃሴቸው ምክንያት የታሰሩ ፖለቲከኞች በአካል ወደ ምክክሩ መጥተው መሳተፍ ስለማይችሉ፤ በምክክሩ እንዴት ይሳተፉ የሚለውን እየተነጋገርበር ነው ያሉን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ብሌን ገብረ መድህን ናቸው፡፡
በተጨማሪም ኮሚሽነሯ በፖለቲካ ምክንያት የታሰሩ ነገር ግን በአጀንዳነት ይያዝልን የሚሉት ሃሳብ ያላቸው እስረኞች አጀንዳቸውን ከእስር ቤት ሆነው እንዲልኩ ለምን አልተደረገም በሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ እስረኞቹ በምን መንገድ ይሳተፉ የሚለው ገና አልተወሰነም እየተመከረበት ነው፤ ነገር ግን ሃሳቦቻቸው በፓርቲዎቻቸው በኩል ይካተታሉ ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ካሳለፍነው ግንቦት 21 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታ 7 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የቆየው አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በነገው እለት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ምንታምር ፀጋው
Коментарі