top of page

ጥር 16፣2016 - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ትኬቶችን በሳፋሪኮም ኤም-ፔሳ በኩል መግዛት የሚያስችል ሰምምነት ተፈረመ

  • sheger1021fm
  • Jan 25, 2024
  • 1 min read

በሳፋሪኮም ኤም-ፔሳ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ትኬቶችን መግዛት የሚያስችል ሰምምነት ተፈረመ፡፡


ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የንግድ ዘርፍ ዋና ሀላፊ አቶ ለማ ያዴቻ እና የሳፋሪኮም ኤም-ፔሳ የዲጂታል ፋይናንስ ዋና ሃላፊ ፖውል ካቫቩ ተፈራርመውታል፡፡


በስምምነቱ መሰረት የሳፋሪኮም ኤም-ፔሳ ደንበኞች የጉዞ ትኬቶቻቸውን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሞባይል መተግበሪያ፣ ድረ-ገጽ ወይም በአየር መንገዱ አለም አቀፍ የጥሪ ማእከል በኩል እንዲገዙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡


ይህም ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ቀልጣፋ እና አስተማማኝ ክፍያዎችን ለመፈጸም ያስችላል ተብሎለታል።


የሳፋሪኮም ኤም-ፒኤሳ ደንበኞች ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ አየር የጉዞ ትኬቶችን ፣ የበረራ ለይ ግዢዎችን፣ የሻንጣ ክፍያ እና ሌሎች ከፍያዎችን በቀላሉ ማከናወን ይችላሉ ተብሏል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page