top of page

ጥር 23፣ 2015- የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ወደ ዩክሬይን F-16 የጦር ጄቶችን አልልክም አሉ

  • sheger1021fm
  • Jan 31, 2023
  • 1 min read

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ወደ ዩክሬይን F-16 የጦር ጄቶችን አልልክም አሉ፡፡


ዩክሬይን ባለፈው ሳምንት አሜሪካ አብራምስ ታንኮችን እንደምትሰጣት ቃል ከገባችላት በኋላ F-16 የጦር አውሮፕላኖችንም ማግኘቴ አይቀርም ብላ እንደነበር ቻይና ኦርግ ድረ ገፅ ፅፏል፡፡


ባይደን ለዩክሬይን አብራምስ ታንኮችን ለመስጠት ቃል የገቡላትም ከብዙ ማቅማማት በኋላ ነበር፡፡


አሁንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዩክሬይንን እንደው በሌላ በሌላው እንረዳሻለን እንጂ F-16 የጦር አውሮፕላኖችን አንሰጥሽም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


የዩክሬይን ሹሞች ከ F-16 በተጨማሪ እጅግ ዘመን አፈራሽ የሆኑ ሌሎች የምዕራባዊያን አገሮችን የጦር አውሮፕላኖችንም በእጃቸው ለማስገባት ጓጉተው እንደነበር ይነገራል፡፡


ፖላንድ ግን በሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ፈቃድ ካገኘች ለዩክሬይን ዘመን አፈራሽ የጦር ጄቶችን ለመስጠት ማሰቧ ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page