top of page

ጥር 23፣ 2015- የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በአገሪቱ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቆራረጡ ምክንያት የአደጋ ጊዜ አዋጅ የማሳወጅ እቅድ እንዳላ

  • sheger1021fm
  • Jan 31, 2023
  • 1 min read

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በአገሪቱ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቆራረጡ ምክንያት የአደጋ ጊዜ አዋጅ የማሳወጅ እቅድ እንዳላቸው ተናገሩ፡፡


የአዋጁ መታወጅ መንግሥት ችግሩን ለማቃለል በቂ ሐብት ማሰባሰብ እንደሚያስችለው ብሉምበርግ ፅፏል፡፡


በደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቆራረጡ የቆየ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ደግሞ እየባሰበት መምጣቱ ይነገራል፡፡


በአገሪቱ ከ90 በመቶ በላይ ኤሌክትሪክ የሚያቀርበው በምህፃሩ (ኤስኮም) የተሰኘው መንግሥታዊው ኩባንያ ነው፡፡


ኩባንያው በስራ ማስኪያጃ እጥረት እና በብልሹ አሰራር እየተፈተነ ነው ይባላል፡፡


በዚያ ላይ ምዝበራ እና ያረጁ የኤሌክትሪክ አውታሮች የችግሩ ሌሎቹ ምክንያቶች ናቸው ይባላል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page