top of page

ጥር 24፣ 2015- የብራዚል የቀድሞ ፕሬዘዳንት ጂየር ቦልሶናሮ በአሜሪካ የ6 ወራት ቪዛ እንዲፈቀድላቸው ጠየቁ

  • sheger1021fm
  • Feb 1, 2023
  • 1 min read

የብራዚል የቀድሞ ፕሬዘዳንት ጂየር ቦልሶናሮ በአሜሪካ የ6 ወራት ቪዛ እንዲፈቀድላቸው ጠየቁ፡፡


ቦልሶናሮ የመንፈቅ ቪዛ እንዲሰጣቸው ለአሜሪካ መንግስት ጥያቄ ማቅረባቸውን ጠበቃቸው መናገራቸው አናዶሉ ፅፏል፡፡


እንደሚባለው ጂየር ቦልሶናሮ ደጋፊዎቻቸውን ለአመፅ በማነሳሳት በብራዚል በሕግ ይፈለጋሉ፡፡


የቦልሶናሮ ነውጠኛ ደጋፊዎች ከጥቂት ሳምንታት በፊት በርዕሰ ከተማዋ ብራዚሊያ መንግስታዊ ተቋማትን በመውረር መጠነ ሰፊ ውድመት አድርሰዋል፡፡


በቦልሶናሮ ደጋፊዎች ከተወረሩ መካከል የፓርላማው እና የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሕንፃ እንዲሁ ቤተ መንግስቱ ይገኙበታል፡፡


ፕሬዘዳንት ሉላ አናሲዮ ዴ ሲልቫ የአመፁ ጠንሳሾችም ሆኑ ተሳታፊዎች ሕግ ፊት ቀርበው የእጃቸውን ያገኛሉ ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page