top of page

ጥቅምት 15፣2017 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • sheger1021fm
  • Oct 25, 2024
  • 1 min read

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዘዳንት ሲሪል ራማፎሣ የፍልስጤማዊያኑን መሪ ማሐሙድ አባስን ምንግዜም ከጎናችሁ ነን አሏቸው፡፡


ራማፎሣ እና አባስ ከብሪክስ ጉባኤ በተጓዳኝ በካዛን የገፅ ለገፅ ንግግር ማድረጋቸውን TRT አፍሪካ ፅፏል፡፡


ደቡብ አፍሪካ እስራኤል በጋዛ የጦር ዘመቻዋ የዘር ማጥፋት እየፈፀመች ነው በሚል በተባበሩት መንግስታት ችሎት ፊት እንደገተረቻት መረጃው አስታውሷል፡፡


አፍሪካዊቱ አገር ፍልስጤማውያን የነፃ አገር ባለቤቶች መሆን አለባቸው የሚለው እምነቷ የጠነከረ መሆኑ ይነገራል፡፡


ማሐሙድ አባስም ለዚህ ሁሉ ደቡብ አፍሪካን በእጅጉ ማመስገናቸው ተሰምቷል፡፡


ደቡብ አፍሪካ ነባር የብሪክስ አባል ሀገር ነች፡፡


የሱዳን መንግስት ጦር በሴናር ግዛት የምትገኘውን የአል ሰዱኪ ከተማን መልሶ በእጁ አስገባት፡፡


ቀደም ሲል ዲንዴርን ከተማ መያዙን ሱዳን ትሪቢዩን አስታውሷል፡፡


ጦሩ አል ሱኪን የያዛት አል ዲንዴርን በተቆጣጠረ 24 ሰዓታት ባልሞላ ጊዜ ነው ተብሏል፡፡


በተለይም አል ዲንዴር የሴናር እና የገዳሪፍ ግዛቶችን የምታገናኝ ቁልፍ ከተማ እንደሆነች ተጠቅሷል፡፡


በሴናር ግዛት ተፋላሚዎቹ የሚያካሂዱት ውጊያ ከበድ ያለ ነው ተብሏል፡፡


የሱዳን መንግስት ጦር እና በምህፃሩ RSF የተሰኘው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ጦርነት ማካሄድ ከጀመሩ ከአመት ከመንፈቅ በላይ ሆኗቸዋል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page