ጥቅምት 23፣2016 -ዶክተር ለገሰ ቱሉ ረሃብ እነደተከሰተ የሚነገረው ወሬ ሀሰት ነው ቢሉም የተለያዩ ሹሞች ሰዎች በረሃብ እየሞቱ መሆኑን እየተናገሩ ነው
- sheger1021fm
- Nov 3, 2023
- 1 min read
የመንግስት የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በኢትዮጵያ ረሃብ የተከሰተባቸው ቦታዎች እንዳሉ ተደርጎ የሚነገረው ወሬ ሀሰት ነው ሲሉ አስተባብለዋል፡፡
ድርቅ እንጂ ረሃብ የለምም ይላሉ፡፡
ይሁንና ሸገር ያነጋገራቸው የተለያዩ አካባቢዎች የመንግስት ሹሞች በረሃብ ምክንያት የሰዎች እና የእንሰሳት ህይወት እያለፈ መሆኑን እየተናገሩ ነው፡፡
ረሃብ ላይ ነን የሚሉ ተፈናቃዮችም በርካታ ናቸው፡፡
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Comentarios