top of page

ጥቅምት 6፣2017 - ከሰሞኑ በአዲስ አበባና አካባቢዋ እየጣለ ያለው ዝናብ ወቅቱን ያልጠበቀና ጉዳትም ሊያስከትል እንደሚችል የ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 16, 2024
  • 1 min read

ከሰሞኑ በአዲስ አበባና አካባቢዋ እየጣለ ያለው ዝናብ ወቅቱን ያልጠበቀና ጉዳትም ሊያስከትል እንደሚችል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡


በኢንስቲትዩቱ የትንቢያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር አሳምነው ተሾመ(ዶ/ር) ከሰሞኑ እየጣለ ያለው ዝናብ ያልተለመደ መሆኑንና በተለይም በደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ባለፈው ነሐሴ 2016 ዓ.ም በበጋ ወቅት የሚኖረውን ትንቢያ በሰጠበት ወቅት በተለይም አዲስ አበባን ጨምሮ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ቤኒሻንጉል ክልሎችና በመካከለኛውና በምስራቅ ኦሮሚያ ትንቢያ ሰጥቶ እንደነበር ያስታወሱት ባለሙያው ከሰሞኑ የተከሰተውም ይኸው ነው ብለዋል፡፡


ባለፈው ክረምት እነደነበረው አይነት ጎርፍ የማስከተል አቅም አይኖረው የተባለው ዝናብ መሰብሰብ ያለባቸውን የደረሱ ሰብሎችን ካገኘ ሊያበላሽ እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡


ወቅቱን የጠበቀ አይደለም፣ ተፅእኖውም ከክረምት የቀጠለ ነው የተባለው ዝናብ ምክንያቱ የላኒኖ ተፅዕኖ ነው ይላሉ፡፡


የአየር ትንቢያ መረጃዎቹ እንደሚያሳዩት የዝናቡ ስርጭት በሚቀጥሉት 10 ቀናትም ይቀጥላል፤ በተለይ የደረሱ ሰብሎች ያሏችሁ ጠንቀቅ በሉ ተብላችዋል፡፡


አዲስ አበባን ጨምሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች የዝናብ ሥርጭቱ ይቀጥላል መባሉን ከሀላፊው ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን በድምፅ ለማድመጥ ይህንን ማስፈንጠሪያን ይጫኑ... https://tinyurl.com/yhmjyvvy


ምንታምር ፀጋው


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page